Рет қаралды 668,629
በክርስቶስ ኢየሱስ ለመሆን የበቃችሁት ከእርሱ የተነሣ ነው፤ እርሱ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበባችን፣ ጽድቃችንና ቅድስናችን፣ ቤዛችንም ሆኖአል። እንግዲህ፣ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው፤ “የሚመካ በጌታ ይመካ።”
1 ቆሮንቶስ 1:30 - 31
It is because of him that you are in Christ Jesus, who has become for us wisdom from God-that is, our righteousness, holiness and redemption. Therefore, as it is written: “Let the one who boasts boast in the Lord.”
1 Corinthians 1:30-31
ይሄ ቢሆንልኝ ብዪ የምመኘው
ህልሜ እውን ሆኖ መች ነው የማየው
ብዪ የማስበው የማልመው ነገር
ተሰጥቶኛል አንተን ያገኘሁኝ ቀን
ተራራ አልወጣሁ ወይ አልወረድኩኝ
ግን እንዲሁ በፀጋህ ስለወደድከኝ
ከምለምነው እና ከማስበው በላይ
ቤት ሰርተህልኛል በሰማይ
አንተ ክብሬ ነህ አንተ ጥበቤ
ቅድስናዪ የሱስ ቤዛዪ
ምን አለኝ የምሻው ከእንግዲህ
ሁሉም ተሰጥቶኛል በስምህ
ፍቅርህን እያየሁ ሁሌ አመልክሀለሁ
የእግዚአብሔር ልጅ ወድሃለሁ
አሁን ያንተ የሆነው ሁሉ የኔ ነው
ፍለጋ አልወጣም ማዶ ማዶ እያየሁ
የተቀበልከውን ሁሉ ስለሰጠኸኝ
ከአንተ የተነሳ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ
የተቀበልከውን ሁሉ ስለሰጠኸኝ
ካንተ የተነሳ የንጉስ ልጅ ነኝ
ነጻ ወጥቻለሁ ከሀጥያት አበሳ
ባርነቴ ቀርቷል ካንተ የተነሳ
አንተ መሀል ገብተህ እኔን አስመለጥከኝ
ውርደቴን ስድቤን ሞቴን ወሰድክልኝ