Рет қаралды 62,693
በባቢሎንም የነበሩ በሰናዖር ምድር ሰፊ ሜዳ አግኝተው ሳንሞት ስም ማስጠሪያ ግንብ እንገንባ ብለው መክረው ታላቅ ግንብ ገነቡ፡፡ አለቃቸው ናምሩድ ይባላል እሱም ሞትን የሚያመጡብን ሥላሴ ናቸውና እነርሱን ወግተን ሞትን እናርቅ አላቸው፡፡ ከዚያ ጦር እየሰበቁ ይወረውሩ ጀመር ሰይጣንም ከደመና በምትሀት ደም እየቀባ ይልክላቸዋል፡፡ እነሱም ደሙን እያዩ አሁን አብን ወጋነው አሁን ወልድን ወጋነው ይሉ ጀመር፡፡ ሥላሴ ምንም እንኳ ምሕረታቸው የበዛ ቢሆኑም ዲያብሎስ ስለሠለጠነባቸው ‹‹ኑ እንውረድ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው›› ብለው ቋንቋቸውን ለያዩባቸው፡፡ ውኃ ሲለው ጭቃ ጭቃ ሲለው ደንጊያ የሚያቀብለው ሆነ እንዲህ የማይግባቡ ቢሆኑ ተበታትነዋል፡፡ ባለማስተዋል የሠሩትንም ሕንፃ ዓመጻ ነፋስ ጠራርጎ አጥፍቶታል፡፡ ዘፍ. 11፥1-9