Рет қаралды 2,682
የቀደመው ታኅሣሥ ወር፣ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መልካም ዜና አስደምጦ ያለፈ አልነበረም። አገሪቷ፣ ከግል እና ከይፋዊ አበዳሪዎቿ ከተበደረቻቸው ብድሮች መካከል፣ ለኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ለስኳር ፋብሪካዎች ግንባታ በሚል ቦንዷን አስይዛ የተበደረችው አንድ ቢሊየን ዩሮ ያልተጠበቀ መዘዝ ይዞባት መጥቷል። የዚኽ አንድ ቢሊየን ዩሮ ወለድ የሆነውን ሠላሳ ሦስት ሚሊየን ዶላር መክፍል ያልቻለችው ኢትዮጵያ፣ የእፎይታ ጊዜ ቢጨምርላትም ሳትከፍል ቀነ-ገደቡ ተጠናቋል። ይኽም የብዙ ተደማጭ ሚዲያዎችን የፊት ገፅ የሸፈነ ርዕሰ-ጉዳይ ሆኖ ሰንብቷል። ዋዜማም በዚኹ ጉዳይ፣ የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎችን በ”ከ8ኛው ወለል” ስቱዲዮዎ ጋብዛ አወያይታለች፤ ያድምጡት፣ ያተርፉበታል።