Рет қаралды 108
#subscribe #share #የመንፈስ_ፍሬዎች በገላቲያ 5:22 #የመንፈስ_ፍሬዎች ገላትያ ዛሬ ቱርክ እየተባለች የምትጠራ ሀገር ውስጥ የምትገኝ አንድ አውራጃ ናት፡፡ ገላትያ በቱርክ ሀገር መሐል ከሰሜን እስከ ደቡብ የሚገኘው ነው፡፡ ይህች የገላትያ ከተማ ለአንጸኪያ፣ ለኢቆንዮን፣ ለልስጥራንና፣ ለደርቤን ከተሞች አዋሳኝ ናት፡፡ እነዚህ ከተሞች ቅዱስ ጳውሎስ ለመጀመሪያ ጊዜ ወንጌልን ለመስበክ ሲወጣ የጎበኛቸውና ያረፈባቸው ከተሞች ናቸው፡፡ ሐዋ. 16.6፣ 18:23
ስለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚናገረው አምላካዊ የምሥራች ቃል በሁሉም ሥፍራ በሚነገርበት ወቅት ከአይሁድ ወገን ያልሆኑ ሰዎች እያመኑ በሄዱ መጠን ክርስቲያን ለመሆን የሙሴን ሕግ መፈጸም ያስፈልጋል? ወይስ አያስፈልግም? የሚል ጥያቄ በስፋት ይነሳ ጀመር፡፡ ያኔ ነው ቅዱስ ጳውሎስ ክርስቲያን ለመሆን የሙሴን ሕግ መፈጸም አያስፈልግም፡፡ በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ሕይወት ለማግኘት መሠረቱ እምነት ነው፡፡ ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት ሊጸድቁ የሚችሉት በእውነተኛ እምነትና በመልካም ተግባር መሆኑን ቅዱስ ጳውሎስ በስፋት ማስተማር በመጀመሩ በዙዎች ወደ እምነት መጡ፡፡ የገላትያ መልዕክት በይዘቱ ክርስቲያኖች ትሑት /መንፈሰ ሰበራ/ ሲያደርግ በሌላ ጎኑ ደግሞ ለለውጥ የምንጥር ቆራጥና ታማኝ አማኞችና አገልጋዮች እንድንሆን ይረዳናል፡፡
የገላትያ መልዕክት የአጀማመር
የገላትያ መልዕክት 6 ምዕራፎች አሉት፡፡ ሲጀምርም፡-“በኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታንም ባነሳው በእግዚአብሔር አብ ሐዋርያ የሆነ እንጂ ከሰዎች ወይም በሰው ያልሆነ ጳውሎስ ከእኔም ጋር ያሉት ወንድሞች ሁሉ ወደ ገላትያ አብያተ ክርስቲያናት፤ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን፣ ክፉ ከሆነ ከአሁን ዓለም ያድነን ዘንድ እንደ አምላካችንና እንደአባታችን ፈቃድ ስለኃጢአታችን ራሱን ሰጠ፡፡ ለአብ ከዘለአለም እስከ ዘለአለም ክብር ይሁን አሜን”፡፡ እያለ ይቀጥልና በቁጥር 8 ላይ “ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን” ይላል፡፡ አቤት በዚህ እርግማን ውስጥ ስንቱ ይገኝ ይሆን? … ይሰውረን፡፡
#የመንፈስ_ፍሬዎች
1.ፍቅር
2.ደስታ
3.ሰላም
4.ትዕግስት
5.ቸርነት
6.በጎነት
7.እምነት
8.የውሃት
9.ራስን መግዛት
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየን!
#Absera_Tube