Muler Entertainment ኣብ ቅድስቲ ማርያም ኲሓ ናይ ቂኔ ምርኢት ንሃገረ ስብከት መቀለ

  Рет қаралды 28

Muller Entertainment

Muller Entertainment

Күн бұрын

Muler Entertainment - ሙሉር ኢንተርተይመንት
ዩቲብ ቻነል!
🔔On this channel.you'll find musics,Live performances,new music
videos,social media tips videos,i upload three videos evrey week.
እንኳዕ ናብ ሙሉር ኢንተርተይመንት ብሰላም መፃእኹም። ኣብዚ ቻናል ደስ ዝብሉ ናይ መድረኽ ስራሕቲ;ድኩመኒትሪ፡ፍልምን፡ሓፂር ኮሞዲ፡ሓደሽቲ ትግርኛ ቪድዮ ደርፍታትን ንምርኣይ ሳብስክራይብ ብምግባር ናይ ደወል ምልክት ብምንኻእን ቤተሰብ ሙሉር ኢንተርተይመንት ይኹኑ ስለ ዝመፃእኹም የመስግን::🔔
🔔social media_ንምክትታል እትደልዩ🔔
1️⃣facebook=Muler Entertainment
2️⃣WhatsApp =Muler Entertainment
3️⃣Tik tok=Muler Entertainment
4️⃣Telegram = Muler Entertainment
5️⃣ lnstagram =Muler Entertainment
6️⃣Gmail =mulugetamuruts12@gmail .com
፩፦ « መጋባት በሁሉ ዘንድ ክቡር ነው፤» ዕብ ፲፫፥፬
ጋብቻን ባርኮና ቀድሶ ለሰው ልጅ የሰጠው እግዚአብሔር ነው። በመሆኑም ጋብቻ የእግዚአብሔር ጸጋ ነው። ስለዚህ በዓይን ምኞት ተጋርደው፥ በሥጋ ፍላጐት ተነድተው ፥ በስሜት ፈረስ ጋልበው ፥ የሚገቡበት ሳይሆን ፦ በጸሎት እና በምልጃ ፈቃደ እግዚአብሔርን ጠይቀው የሚፈጽሙት ታላቅ ምሥጢር ነው።
ጋብቻ የሰው ሁሉ ሕልም ነው። የማይመኘው፥የማይፈልገው የለም። የሰው ሁሉ ጸሎት፥ የሰው ሁሉ ስእለት ነው። ለመሆኑ፦ ህልሙ የተፈታለት ፥ ጸሎቱ የደረሰለት ፥ ስዕለቱ የሰመረለት ስንቱ ይሆን? ያላገባው ይናፍቃል ፥ ያገባው ደግሞ ያማርራል። ከጋብቻ በፊት « መልአክ » የተባለ የትዳር ጓደኛ ከጋብቻ በኋላ «ሰይጣን» ይባላል። «እኔ የመረጥኩትን ካላገባሁ እሰቀላለሁ፤» እንዳልተባለ «ካልተፋታሁ መርዝ እጠጣለሁ፤» ለማለት ችግር የለም። ከጋብቻ በፊት ምክር ላለመስማት አሳብ ላለመቀበል፦ «ስለ እኔ ማንም አያገባውም፤» ተብሎ በር እንዳልተዘጋ ሁሉ ከጋብቻ በኋላ ግን ጣልቃ የማያስገቡት ሰው የለም ፤ «ምን በወጣህ ፥ ምን በወጣሽ፤» የሚለውን ፈጥኖ ለመቀበል በሩ ለሁሉም ክፍት ነው።
፪፦ ጋብቻ እንዴት ተጀመረ?
ጋብቻ በአዳምና በሔዋን እንደተጀመረ የጎላ፥ የተረዳ ፥ የታወቀ ነገር ነው። «ተባዕተ ወአንስተ ገብሮሙ፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፤ » እንዲል፦ አዳም ሲፈጠር ሔዋን በውስጡ ነበረች። ዘፍ ፩፥፳፰። ይህም በባህርዩ ነበረች ማለት ነው። አንድ አካል፥ አንድ ሥጋ ከሚያሰኛቸው ምሥጢር አንዱና ዋነኛውም ይኸው ነው።
ጋብቻ የተጀመረው በአዳም ጥያቄ ነው፤ ጥያቄዎም የኅሊና ማለትም ውሳጣዊ ነበር። ምክንያቱም፦ ከላይ እንደተ መለከትነው፦ የትዳር ጓደኛው በውስጡ ስለነበረች ነው። « እግዚአብሔር አምላክም፦ ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት፥አለ፤»ይላል። እግዚአብሔር እንዲህ ማለቱ፦ በአዳም ኅሊና ውስጥ ይህ ጥያቄ እንደሚነሣ ስለሚያውቅ ነው። መናገሩም ለአዳም ኅሊና እንጂ ፥ ሔዋን ለአዳም እንደምትፈጠርለት አስቀድሞ በእግዚአብ ሔር ዘንድ የተወሰነ ነው።
እግዚአብሔር፦ የምድር አራዊትንና የሰማይ ወፎችን ሁሉ፦ ሕያው ነፍስ ላለውም ሁሉ ስም ያወጣላቸው ዘንድ ወደ አዳም አመጣቸው። ይላል። ሂደቱም እንደሚከተለው ነው። እግዚአብሔር ዓርብ በነግህ አዳምን ከፈጠረ በኋላ ቅዳሜ መፍጠሩን ተወ። እሑድ እንስሳትን አራዊትን አመጣለት ፤ ሰኞ ማክሰኞ አዕዋፋትን አመጣለት፤ ረቡዕ በየብስ የተጠፈጠሩ ፍጥረታትን አመጣለት፤ ሐሙስ በባሕር የተፈጠሩ ፍጥረታትን አመጣለት፤ ለሁሉም ስም አወጣላቸው። በዚህን ጊዜ አዳም፦ ሁሉም ተባዕትና አንስት (ወንድና ሴት) መሆናቸውን አይቶ ፦ « ከእኔ በቀር ብቻውን የተፈጠረ የለም፤» ብሎ አዘነ። «ነገር ግን ለአዳም እንደ እርሱ ያለ ረዳት አልተገኘለትም ነበር ፤» ይላል።
፪ ፥፩ ፦ ሐዘነ አዳም፤
እግዚአብሔር አዳም እስኪያዝን የጠበቀው ያለ ምክንያት አይደለም። አጭቶ፥ ወድዶ፥ ፈቅዶ እንዲገባበት ነው። ይህም፦ ወደፊት ሔዋን ስታሳስተው ለኃጢአቱ እግዚአብሔርን ምክንያት እንዳያደርግ ይጠብቀዋል። አዳም ሳያዝን ሔዋንን ፈጥሮለት ቢሆን ኖሮ፦ « ይኼ እግዚአብሔር ፍጠርልኝ ሳልለው ሔዋንን ፈጥሮ ምክንያተ ስሕተት ሆነችብኝ፤» ባለ ነበር። እግዚአብሔር ግን አዳም እስኪፈልግ ጠብቆ ፦ ከጎኑ አንዲት አጥንት ወስዶ ሴት አድርጎ ሠራለት። አዳምም፦ «ይህች አጥ ንት ከአጥንቴ ናት ፥ ሥጋም ከሥጋዬ ናት፤ እርስዋ ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል። ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፥ ከሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።» ብሎ እግዚአብሔር የሰጠውን በጸጋ ተቀበለ። ዘ፪፥፲፰-፳፬።
፪፥፪፦ አንድ ሥጋ መሆን፤
አዳምና ሔዋን በጋብቻ አንድ አካል መሆናቸው፦ ሔዋን ከአዳም የጎን አጥንት በመፈጠሯ ብቻ አይደለም። አንድ ክብር በመውረስም ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ፦ «እናንተ ባሎች ሆይ ፥ ደካማ ፍጥረት ስለሆኑ ከሚስቶቻችሁ ጋር በማስተዋል አብራችሁ ኑሩ፤ ጸሎታችሁ እንዳይከለከል አብረው ደግሞ የሕይወትን ጸጋ እንደሚወርሱ አድረጋችሁ አክብሩ አቸው።» ያለው ለዚህ ነው። ፩ኛ ጴጥ ፫፥፯። ከዚህም ሌላ አንድነታቸው አንድ ልብስ በመልበስ ነው። ፈቃደ ሥጋቸው በጠ የቃቸው ጊዜም በግብር አንድ ይሆናሉ። ወንድ ቢወለድ ያንተ ነው፥ ሴት ብትወለድ ያንቺ ነው አይባባሉም። ሁለት ሆነው አንድ ልጅ ያስገኛሉ። አንድም፦ ከእናት ደም ፥ ከአባት ዘር ተከፍሎ አንድ ሰው ሁኖ ይወለዳል።
፪፥፫፦ ሁለቱም ዕራቁታቸውን ነበሩ፤
አዳምና ሔዋን ከዚህ ዓለም ልብስ ዕራቁታቸውን ነበሩ። አዳም ከሱፍ የተሠራ ሙሉ ልብስ አልለበሰም ፥ ሔዋንም ዋጋው እጅግ ውድ የሆነ ቬሎ አልለበሰችም። መጫሚያም አልነበራቸውም። የጣት ቀለበት ፥ የጆሮ ጌጥ ፥ የእጅ አንባር ፥ የእግር አልቦ አላደረጉም። ቅዱስ ጴጥሮስ ይኽንን ይዞ ነው፥ «ለእናንተም ጠጉርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ፥ ወይም ዋጋው ብዙ የሆነ ልብስን በመጐናጸፍ የውጭ ሽልማት አይሁንላችሁ። ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ ፥የዋህና፦ ጸጥ ያለ መንፈስ ያለው ፥ የማይጠፋና የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ፤» ያለው። ፩ኛ ጴጥ ፫፥፫። ሐዋ ርያው ቅዱስ ጳውሎስም፦ « እንዲሁም ደግሞ ሴቶች በሚገባ ልብስ ከእፍረትና ራሳቸውን ከመግዛት ጋር ሰውነታቸውን ይሸ ለሙ፤ እግዚአብሔርን እንፈራለን ለሚሉት ሴቶች እንደሚገባ ፥ መልካም በማድረግ እንጂ በሹሩባና በወርቅ ወይም በዕንቊ ወይም ዋጋው እጅግ በከበረ ልብስ አይሸለሙ።» ብሏል። ፩ኛ ጢሞ ፪፥፱።
አዳምና ሔዋን ብርሃን ለብሰው ስለነበር ዕራቁታቸውን ሆነው አይተፋፈሩም ነበር። «ብርሃን የተሰወረውን ይገል ጻል እንጂ የተገለጸውን ይሰውራልን?» ቢሉ ፥ እግዚአብሔር ሰውር ካለው ይሰውራል። አንድም አዳምና ሔዋን ከልብሰ ኃ ጢአት ዕራቊታቸውን ነበሩ። ( ኃጢአት ፥ በደል አልነበረባቸውም) ማለት ነው። አይተፋፈሩም ነበር ፥ ማለትም ፦ ለሰባት ዓመታት ኃፍረተ ነፍስ አልነበረባቸውም ነበር ፥ ማለት ነው።
፫፦ የጋብቻ ዓላማ፤
የጋብቻ ዓላማዎች ሦሰት ናቸው። የመጀመሪያው። « የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት፤» እንዲል፦ ለመረዳዳት ነው። መረዳዳት ሲባልም በሥጋ ብቻ አይደለም በነፍስም ጭምር ነው። ለሥጋቸው በሥራ ሲረዳዱ ለነፍሳችው ደግሞ በጸ ሎት ይረዳዳሉ። ለምሳሌ፦ ይስሐቅ፦ ሚስቱ ርብቃ ለሃያ ዓመታት መክና ልጅ አልወለደችለትም ነበር። በዚህም ምክንያት ስለ ርብቃ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ፥ እግዚአብሔርም ተለመነው፥ ርብቃም መንታ ፀነሰች ይላል። ዘፍ ፳፭ ፥፳፩። ሁለተ ኛው በፍትወተ ሥጋ ላለመቸገር ነው። ሦስተኛው ደግሞ፦ «ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው ፥እግዚአብሔርም ባረካቸው ፥እንዲህም አላቸው፦ ብዙ ተባዙ ፥ምድርንም ሙሉአት።» እንዲል፦ ዘር ለመተካት ነው። ዘፍ ፩፥፳፰። እነዚህም እንደ ሦስት ጉልቻዎች የሚቆጠሩ ናቸው።

Пікірлер
А что бы ты сделал? @LimbLossBoss
00:17
История одного вокалиста
Рет қаралды 9 МЛН
啊?就这么水灵灵的穿上了?
00:18
一航1
Рет қаралды 57 МЛН
规则,在门里生存,出来~死亡
00:33
落魄的王子
Рет қаралды 32 МЛН
🏃‍♂️አነጋጋሪው የዶክተሩ ቪዲዮ በሔቨን ጉዳይ @awtar_media
25:04
Awtar Media አውታር ሚዲያ
Рет қаралды 18 М.
А что бы ты сделал? @LimbLossBoss
00:17
История одного вокалиста
Рет қаралды 9 МЛН