Рет қаралды 3,308
የምጽአት ምልክቶች
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሳለ ደቀመዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው የዳግም ምጽአት ምልክትን ጠይቀውታል። እርሱም አስቀድሞ «ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ» ካለ በኋላ የሚከተሉትን ምልክቶች ገልጾላቸዋል።
፠ብዙ ሀሰተኛ ነቢያት ይነሳሉ ፣
፠ብዙ ሀሰተኛ ክርስቶሶች ይነሳሉ ፣
፠ታላቅ ክሕደት ይሆናል ፣
፠በብዙዎች ዘንድ ፍቅር ይቀዘቅዛል ፣
፠የጦርነት ፣ የርኃብ ፣ የቸነፈር የምድር መናወጥ ወሬ መሰማት ፣
፠ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥት በመንግሥት ላይ መነሳሳት ፣
፠ክርስቲያኖች በአሕዛብ የተጠሉ መሆን ፣
፠የብዙዎች ለሞት ተላልፈው መሰጠት ፣
፠የብዙዎች ከእውነት መንገድ መሰናከል ፣
፠የጥፋት ርኲሰት በተቀደሰችው ስፍራ መታየት፣
፠የተመረጡት እስኪስቱ ድረስ ድንቅ ተአምራት መደረግ ፣ (ማቴ ፳፬ የመከራ ዘመን ይሆናል)
፠«ስለ ሕዝብ ልጆች የሚቆመው ታላቁ ሚካኤል ይነሳል።» (ዳን ፲፪ ፥ ፩ )
፠የአመጽ ሰው የክርስቶስ ተቃዋሚ መነሳት ፣ (፪ ተሰ ፪ ፥ ፫ )
፠የአውሬው የስድብ አፍ በገልጽ በብዙዎች ላይ መገለጽ (ራእይ ፲፫፥ ፭ ) ፣ ወዘተ