Рет қаралды 20,098
🛑👉 ይህች መጽሐፍ ካለችበት ቦታ እስከ ዘለአለም ድረስ ምህረት ቸርነት ተድላ ደስታ ጥጋብ ይሁን ስምሽ በተጠራበት ሥዕልሽም ባለበት መታሰቢያሽም በተደረገበት በስምሽም በሚጸለይበት ቦታ ሁሉ 🌹እኩያን አጋንንት አይቀርብም በረቂቅ ሰዉን የሚያሠቃዩ ጸሊማን ዛር ዉላጆችም ይርቃሉ ይህችን መጽሐፍ በክበር ይዞ ለሚጸልይ የጨለማ ኀይል አይጋርደዉም ርኩሳን መናፍስት የቀትር አጋንንት ሊቀርቡት አይችሉም
በሌሊት በህልም የሚያስደነግጡ በማዓልት በእሾህ መዉጋት ቢሆን በእንቅፋት የሚመሰሉ በእንጀራ ማሳነቅ ወይም በዉሃና በጠላ ትንታ የሚመሰሉ በስካር በቁጣ የሚመሰሉ ልብን በመፋቅ በቃር የሚመሰሉ በጥርስ በሽታ አፍን በማምረር በራስ ምታትና በዓይን ሕመም ቢሆን የሚመሰሉ በልብ ሕመም ወይም በሆድ ቁርጠት የሚመሰሉ በንዳድ (በወባ) በማንቀጥቀጥ ቢሆን የሚመሰሉ በባሕርና በየብስ በእንጨት በድንጋይም ቢሆን የሚመሰሉ በእሳትና በዲን የሚመሰሉ በፈሰቅርና በሰላም ወይም በጠብ ቢሆን የሚመሰሉ በአራዊትና በአዕዋፍ ጩኽት በፀሐይ ሐሩር ወይም በቁርና በአመዳይ በዉርጭ በነፋስ ንዉፅዉዕታ ኃይል ወይም በዉሻ መንከስ የሚመሰሉ በእፉኝት መንደፍ ቢሆን በእሳት ማቃጠል የሚመሰሉ በሌሊት ጨለማ በቀን ብርሃን የሚመሰሉ እሊህ ሁሉ አይቀርቡም ይህችን መጻሐፍ ጸሎት በንጹህ ሕሊና በቅን ልቦና የያዘ የቡዳ ዓይን አያስፈራዉም ይህች መጸሐፍ በምትደገምበት ቦታ ሁሉ እህልን የሚሰልቡ ሰላቢዎች (ሟርተኞች)መድኃኒተኞች የሌሊትና የቀን የዱር አራዊቶች የሚታየዉም ማይታየዉም በረዶ ኩብኩባ አንበጣም ቢሆን ሊቀርቡ አይችሉም በሬም ላምም ቢሆን ቢታመም ይህችን ጸሎት ቢደግሙላቸዉ ክፉ በሽታ አይነካቸዉም ይህችን መጻሐፍ በንጽሕና ለሚይዛት ሁሉ ከደዌ አድነዋለሁ ከሚያስጨንቅ ችግርም እሠዉረዋለሁ ደዌዉም ለሕይወትና ለጤናም ቢሆን እኔ ፈጥኘ አነሳዋለሁ...። t.me/tegteneentseleye