Рет қаралды 23,658
የዮሐንስ ወንጌል ከሦስቱ ወንጌላት የተለየ ነው። የዮሐንስ ወንጌል ስለ ኢየሱስ ያቀረባቸው ታሪኮች ጥቂት ሲሆኑ፣ ብዙ ነገረ መለኮታዊ ውይይቶች አሉት። በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ ታሪኮች የሉም። እዚህ ብዙዎቹ የኢየሱስ ትምህርቶች ከተመሳሳይ ወንጌላት የተለዩ ናቸው። ሦስቱ ተመሳሳይ ወንጌላት ያቀረቧቸው ምሳሌዎች ስለ ኢየሱስ ማንነትና በመስቀል ላይ ስላከናወናቸው ተግባራት ነገረ መለኮታዊ አንድምታዎችን እንድንገምት የሚያደርጉን ሲሆኑ፣ ዮሐንስ ቀን ኢየሱስ መለኮታዊ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነና በእርሱ በማመን የዘላለም ሕይወት እንደሚገኝ በቀጥታ ይገልጽልናል። ዮሐንስ በቃላት አጠቃቀሙ ሳይቀር ለየት ብሎ በመቅረብ፣ እንደ ብርሃን፣ ጨለማ፣ እምነት፣ ኩነኔ፣ ምልክት ከመሳሰሉት ጋር ያስተዋውቀናል።