Рет қаралды 13,686
የመልእክቱ ጸሀፊ እራሱ ጳውሎስ መሆኑ መልእክቱ ይገልጻል 1፣1 እና 3፣1 ይህ መልእክት ኤፌሶንን ጨምሮ ወደ ሌሎች ከተሞች እንዲደርስ የተጻፈ ዘዋሪ ደብዳቤ ሳይሆን አይቀርም 1፣1፣15 6፣21-23 ፤
ጳውሎስ የቆላስያስን መጽሀፍ በጻፈበት ጊዜ በ60 አመተ ምህረት ግድም በሮም እስር ቤት እያለ ይህንን ደብዳቤ ጽፎታል፤ 3፣1 እና 4፣1 6፤20
የኤፌሶን ከተማ በትንሹ እስያ በዛሬዋ ቱርክ ምእራፍ ክፍል ከሚገኙት ከተሞች እጅግ የታወቀች ከተማ ነበረች። ከተማዋ ወደ ኤዥያን ባህር በሚፈሰው የካይስተር ወንዝ ላይ አንድ ወደብ ነበራት ታላላቅ የንግድ መንገዶች አቋርጠው በሚያልፉበት ቦታ ላይ የተመሰረተች ስለሆነች የንግድ ማእከል ለመሆን በቅታለች።
ግሪኮች አርጤምስ ሮማውያን ዲያና የሚሏት ጣአኦት አምላክ ቤተመቅደስ በዚችው ከተማ ይገኝ ነበር። ጳውሎስ በኤፌሶን ሶስት አመት ያህል ተቀምጦ የወንጌል ስርጭት ማእከል አድርጓት ነበር ሐዋርያት 19፤10
በዚያን ጊዜ የነበረችው ቤተክርስቲያን በአንድ ወቅት አድጋ ተስፋፍታ ነበር በኋላ ግን በራእይ 2፤1-7 ያለው ማስጠንቀቂያ ተሰጣት
የመልእክቱ ይዘት እንደ ሌሎቹ የጳውሎስ መልእክቶቸ የስህተት ትምህርት ወይንም ነቀፌታን በተመለከተ የሚያወሳው ነገር የለም። መልእክቱን ሲጽፍ የአንባቢዎችን አድማስ በማስፋት የእግዚአብሔርን የዘላለም እቅድና የጸጋውን ጥልቀት ይበልጥ እንዲረዱና እግዚአብሔር ለቤተክርስቲያን ያለውን ታላቅ ግብ እንዲያደንቁና በዛ ውስጥ መኖር እንዲችሉ ነው ሲሆን ቅዱሳን በክርስቶስ ያላቸውን ህብረትና ማንነት እንዲያውቁና እርስ በእርስም እንደ አካል አንድነትን በመጠበቅ እንዴት መገንባትና ማደግ እንዳለባቸው ለማስተማር ነው።
መጽሀፉን ሁለት መክፈል እንችላለን
፩ኛ ከምእራፍ 1-3 ከክርስቶስ ጋር ስላለን ህብረት
፪ኛ ከምእራፍ 4-6 የክርስቶስ አካል ስለሆነች ቤተክርስቲያን ስለሚኖረን አንድነት