የኦንሊጂሰሱ ቄስ ማንነትና ህልውና ምን ማለት እንደሆነ እንደማያቅ ባደባባይ አመነ | Pastor denies his own teaching Ep 110

  Рет қаралды 2,325

ኦንሊ ጂሰስ Exposing Only Jesus

ኦንሊ ጂሰስ Exposing Only Jesus

Күн бұрын

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን በተለምዶ ኦንሊጂሰስ በመባል የሚታወቀው ቤተእምነት በጣም አደገኛ እና መፅሀፍቅዱስን የሚፃረር የሀሰት እምነት ነው:: ኢየሱስ ኢየሱስ ይላሉ ግን የመፅሀፍ ቅዱሱን ኢየሱስ ፈፅሞ አይቀበሉም:: በወንጌል የሚያምኑ ይመስላሉ ግን የአዲስኪዳንን ወንጌል ፈፅሞ ወደጎን በማለት የራሳቸውን ሰው ሰራሽ ዶክትሪን እና ሀይማኖታዊ ህግጋቶቻቸውን ከመፅሀፍ ቅዱስ በላይ የሚያምኑ ወገኖች ናቸው:: ምእመኖቻቸውም መፅሀፍ ቅዱስን እያነበቡ ስለ አምላካቸው ከማወቅ ይልቅ ድርጅቱ እና የድርጅቱ አስተማሪዎች የሚሉትን ብቻ እንዲቀበሉ ይገደዳሉ:: ኢየሱስን መፅሀፍ ቅዱስ እንደሚለው በቅጡ ሳያምኑ እና ሳይቀበሉ የውሀ ጥምቀት የዘላለም ህይወት ያስገኛል ብለውም ያምናሉ::
በአጭሩ መፅሀፍ ቅዱስን ያለአግባብ በአውዱ እና በስርአቱ ካለማንበብ እና ካለመረዳት የተነሳ የተፈጠረ ድርጅት "CULT” ነው:: ከዚህም የተነሳ የኢየሱስ ማንነት ላይ እጅግ በጣም ስተዋል!
ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን የወልድ እና የመንፈስቅዱስን መለኮታዊነትን የሚክድ ቤተእምነት ነው:: አንዱ እግዚአብሔር ወይም አንዱ መለኮት በአብ ፣ በወልድ እና በመንፈስቅዱስ ተገልጦ እንደሚኖር አያምኑም::
በኦንሊጂሰስ አስተምሮ በስጋ የተገለጠው ቅዱስ የሆነው የእግዚአብሔር ልጅ ሳይሆን እግዚአብሔር አብ ነው:: ኦንሊጂሰሶች የወልድን ዘላለማዊነትም ይክዳሉ:: የእግዚአብሔር ልጅ ለነሱ ከድንግል ማርያም የተወለደ የስጋ ሰውነት ብቻ ነው:: ስጋውንም ሰማያዊ ወይንም መለኮታዊ ከሰማይ የመጣ ስጋ ነው እንጂ የዳዊትን ዘር በስጋ ተካፈለ ብለው አያምኑም:: (ሮሜ 1:3, ሮሜ 9:5, ዕብ 2:14, ራእይ 22:16)
ልጁ ከዘላለም ጀምሮ የነበረ የምድር እና የሰማይ ፈጣሪ መሆኑን ይክዳሉ (ዩሀ 1:3, ዕብ 1:2, ዕብ 1:10, ቆላስያስ 1:16) የእግዚአብሔር ልጅ በስጋ ከመምጣቱ በፊት ከአባቱ ጋር ይኖር የነበረ መሆኑንም አያምኑም (ዮሀ 1:1, ዮሀ 6:38, ዮሀ 16:28, ዮሀ 17:5)
ኦንሊጂሰሶች እባካችሁ ለእግዚአብሔር ቃል ለመፅሀፍ ቅዱስ ስልጣን ሰጥታችሁ ለህሊናችሁ ታማኝ በመሆን ቃሉን ካነበባችሁት ሳታውቁት የወደዳችሁት የመፅሀፍ ቅዱሱ ኢየሱስ በሙላት ይገለጥላቹሀል:: የኢየሱስ ማንነት ላይ መሳሳት ከዘላለም ህይወት መጉደልን ያስከትላል:: 1ኛ ዮሀ 5:12 ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም። እባካቸሁ ከቃሉ ጋር እግዚአብሔር እየተማፀናችሁ ጊዜ አሳ ልፉ:: እግዚአብሔር እውነቱን ይግለጥላችሁ ወዳጆቼ!

Пікірлер: 4
АЗАРТНИК 4 |СЕЗОН 3 Серия
30:50
Inter Production
Рет қаралды 858 М.
У ГОРДЕЯ ПОЖАР в ОФИСЕ!
01:01
Дима Гордей
Рет қаралды 8 МЛН
ቢሾፕ ደጉ ተጨንቀዋል!
35:47
ኦንሊ ጂሰስ Exposing Only Jesus
Рет қаралды 1,6 М.