Рет қаралды 16,563
አማራ ምጡቅ የስነፅሑፍ እና የሙዚቃ ክህሎት ያለው ማህበረሰብ ነው። በዘፈኖቹ ጀግናን ያሞግሳል ፈሪን ያበረታታል ፣ በመዝሙር በመንዙማው አምላኩን ያወድሳል። አማራ ስለ አገሩ ኢትዮጵያ ዘፍኖ ፣ ዘምሮ አይጠግብም ፣ ግን ይህ አመለካከቱ በብሔርተኞች ዘንድ አልተወደደለትም። ይልቁንም ጨቋኝ ፣ ጠቅላይ ፣ የሚሉ ቅፅል ስሞች እየተሰጠው እንዲሸማቀቅ ብዙ ተሞክሯል። የአማራ ስነልቦና ጠንካራ መሆኑ በጀ እንጂ ላለፉት 27 አመታት እንደተከፈተበት ዘመቻ ብዛት አማራ እንደ ህዝብ ድሮ ይጠፋ ነበር።
ከነዚህ ኢትዮጵያዊ ጀግንነትን አጉልተው ከሚያሳዩ የአማርኛ ዘፈኖች አንዱ ይህ በ 1973 ዓ.ም በሂሩት በቀለ የተዘፈነው " ዘሟል ጎራዴው " የተሰኘው ዜማ ዘመን አይሽሬ ነው።