Рет қаралды 28,839
የግብፅ እና የኢትዮጵያ ግንኙነት፡ እጅግ ጥንታዊ እና ውስብስብ ነው። በበጎ ጎኑ ስናየው፡ ግብፅ እና ኢትዮጵያ፡ በክርስትና እምነት በኩል፡ የቆየና የጠበቀ ግንኙነት አላቸው።ከዚያ በተቃራኒ ደግሞ፡ በዐባይ ወንዝ እና በሌሎች ፖለቲካዊ ምክንያቶች፡ ከጥንት ጀምሮ የቆየ ጠላትነትም በመካከላቸው አለ። ለመኾኑ፡ ይኽን ታሪካዊ ጠላትነት አልፈው፡ ኢትዮጵያውያን ነገሥታትና በጥቅሉ ሕዝበ ክርስቲያኑ፡ ከግብፅ ጳጳሳት በማስመጣት ጭምር፡ ግንኙነቱ እንዲቀጥል ይፈልጉ የነበረው፡ ለምን ይኾን?
ሰባት ምክንያቶችን በዚህ ትምህርታዊ ቪድዮ ውስጥ ታገኛላችሁ። እስከመጨረሻው ተከታተሉት!
ዋቢ መጻሕፍት (References):-
የብሉይና የሓዲስ ኪዳን መጻሕፍት
ዶ/ር መስከረም ለቺሳ (2014 ዓ.ም)። የፀሓይ ከተማ። አዲስ አበባ፥ ወይንሸት ማተሚያ ቤት።
“መጽሓፈ ስንክሳር፥ ከመጋቢት እስከጳጕሜን።” አዲስ አበባ፥ ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት፤ 1993።
ተስፋ ሥላሴ ሞገስ (አባ)። ቅዱስ ማርቆስ ኢትዮጵያዊ ነው፤ የተዋሕዶ አንበሣም መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። (አዲስ አበባ፥ 1988)
“ገድለ ቅዱስ ማርቆስ፥ በግእዝና በዐማርኛ።” አዲስ አበባ፥ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤ/ማ/መ/ ማኅበረ ቅዱሳን፤ 2013።
“ገድል ዘቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ።” መሪጌታ ጽጌ ዘርይሁን እና መምህር ዘሚካኤል ገ/ኢየሱስ (ተርጓሚዎች)።አዲስ አበባ፥ አኰቴት አታሚዎች፥ 2005።
“የአቡነ ዜና ማርቆስ ገድል፥ በአማርኛ።” አዲስ አበባ፥ ሳቤላ ማተሚያ ቤት፤ 2005።
ጌጡ ዘለቀ ገ/ማርያም (ሊቀ ትጉኃን)። ክብረ አበው ነገሥት፤ የአበው ቀደምት ነገሥታት ገዳማት እና ቅዱሳን ነገሥታት ወአድባራት ታሪክ (2007 ዓ.ም)።
አዜብ በርሄ (ተርጓሚ) (2008)። ዝክረ ቅዱሳት አንስት ዘተዋሕዶ። አዲስ አበባ፥ ጃጃው አታሚዎች እና ዴቬሎፐርስ ኃ.የተ.የግ.ማ.
Williams, C. (1974). The Destruction of Black Civilization: Great Issues of a Race from 4500 B.C. to 2000 A.D. Chicago: Third World Press.