Рет қаралды 22,002
መልዕክት ከምስራቅ ጉራጌ ዞን እስከ ከተማና ወረዳ ተሿሚዎች...
- ሹመት የህዝብ አደራ ነውና የተሰጣችሁን አደራ በታማኝነትና በቅንነት ህዝባችሁን አገልግሉ...
- በተሰጣችሁ ሹመት አትኮፈሱ: አትመፃደቁ: አንዳንዶች ጠባቂ ይመደብልን የሚል ጥያቄ ሁሉ አቅርባችኋል። ሠው ከኑሮው አልፎ አንተን የሚመለከትበት ጊዜ የለውም።
- ህዝብህን በተለይ አቅም የሌላቸው ድሆች መፍትሔን ፍለጋ ሲመጡ በትህትናና በቅንነት ችግሮቻቸውን ተረዷቸው: አታመናጭቋቸው:አትበድሏቸው: የደሃ እንባ ከባድ ነውና!
- ከሌብነት የፀዳ ሁኑ: ልጆቻችሁ የሌባ ልጅ እንዲባሉ አታድርጉ:
- ስለ ሰዎች ወሬ ሲያቀብሏችሁ: ስለሰማችሁት የግለሰብ ወሬ ላይ ተንተርሳችሁ ሠዎችን ለመጥላት አትቸኩሉ: በራሳችሁ መንገድ አጣሩ: ችግር አለበት ስለተባለ ሰው አቅርባችሁ አውሩት: ምናልባት ችግሩ ያለው ወሬ አቀባዩ ጋር ሊሆን ስለሚችል:
- ወጣቱን ፎርማልና ኢንፎማል ግሩፕ ነው እያላችሁ አትፈርጁ: አትነጣጥሉት: ይህች ሀገር ችግር ሲደርስባት ቀድሞ የሚሰዋላት ወጣቱ ነው። ባይሆን ተቀራርባችሁ ልዪነቶችን በውይይት ፍቱ: ውይይት የማይፈታው ችግር የለምና ወጣቱን አንድ አድርጋችሁ ምሩት:
- ስልክ ሲደወልላችሁ አንስታችሁ አውሩ:ቴክስትም መልሱ
- ለሁሉንም ባለሙያ እኩል እይታ ይኑራችሁ
- በተረፈ ከአዲሱ ከምስራቅ ጉራጌ ዞን እስከ ወረዳና ከተማ የህዝብን አደራ ለማገልገል አዳዲስ የተሾማችሁ: ዳግም ህዝባችሁን ለማገልገል እድሉ ለተሰጣችሁ እንዲሁም በማገልገል ላይ ለነበራችሁ በሙሉ መልካም የህዝብ ማገልገል ጊዜ እንዲሆንላችሁ እየተመኘሁ: "ፍርድ ጎደለ: ደሃ ተበደለ" ወሬ የማንሰማበት ጊዜም
ይሁን...ሠላም! የካህናት አባት !!!
የ30 ዓመታት መታሰቢያ
ዘር ተክቶ ማለፍ ከእግዚአብሔር ታድለው፣
ዛሬ በምድር የሉም አርፈዋል ተጠርተው።
የማይቀር ሆኖ እንጂ ማሰብ እንደገና፣
የእኔ አባት በአምላክ ዘንድ አሉ በምስጋና።
ሞት ጉልበት የለውም ይኽንን አውቃለሁ፣
የትንሣኤው ብርሃን ጋርዷቸው አያለሁ።
ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ሞት ሽሯል፣
አባቴ ይረፉም ከተድላው ገብተዋል።
ለምን እንደማዝን አውቃለሁ መልስ አለኝ፣
ዕለት ዕለት መሰማት የአባት ቃል ናፈቀኝ።
ደሃ ተበደለ ፍርድ ጎድሏል ብለው፣
ዓይኔ አይቷል ሲረዱት የተገፋውን ሰው።
ፍርድ አዋቂ አባቴ ከዓይን ጠፍተው ዛሬ፣
መመገብ ብርቅ ሆነኝ ከምክራቸው ፍሬ።
ቁጣ ተግሣጽ ትምህርት ደግፎ ያቆመኝ፣
ወልጄ ብከብድም ዛሬም አስፈለገኝ።
የአባቴን ምርቃት እሻለሁ አጥብቄ፣
በረከት በዚያ አለ አውቃለሁ ጠንቅቄ።
እንደ ያዕቆብ ልጆች በአባቴ ፊት ቆሜ፣
መመረቅ አምሮኛል እንዲቀለኝ ሸክሜ።
በዕድሜ በዘመኔ እንደ ስንቅ የያዝኩት፣
የማያልቀው ፍሬ ዛሬም ያልጨረስኩት፣
የአባቴ ምክራቸው አለ ከእኔ ጋራ፣
" ሰው ሲወድህ ፍራ ሰው ሲጠላህ ኩራ "
የሚወደድ ምክር የዘመን ስንቅ ነው፣
ይኽንን አንደበት ዛሬ የት ላግኘው?
እግዚአብሔርን ፈሪ የብዙዎች አባት፣
የመቅደስ አገልጋይ ወልደዋል ካህናት።
ከማልረሳው ነገር ዘወትር ከማስበው፣
የአባቴ ይረፉን የደስታ ዕንባ ነው።
አምስት ልጆቹ ለቅዳሴ ገብተን፣
ምስጋና ስናደርስ መንበሩ ፊት ቆመን፣
ፈንቅሎ እየወጣ አልቆም ብሎ ዕንባቸው፣
ያለቅሱ ነበረ ወደ ፈጣሪያቸው።
የካህናት አባት ካህናት ያፈሩ፣
ዘመኑ ቢረዝምም በአምላክ ከተጠሩ፣
ምንኛ በረካሁ ደስ ባለኝ ነበር፣
በአባቴ ፊት ቆሜ የልቤን ብናገር።
ተራዬን ስዘጋጅ ለማቅረብ ምስጋና፣
አባቴን ነጠቀኝ ሞት ድንገት መጣና።
አይበረክት ሆኖ ደግ ሰው በምድር፣
ከዚህ ድንኳን ዓለም ሄደዋል በክብር።
ጠሪው ክርስቶስ ነው እርሱ እንደወደደ፣
በሰማይ በምድር ሁሉን አደረገ።
በዓለም ላይ ያለውን ይኽንን ፈተና፣
ሳያዩት አለፉ አምላክ ፈቅዷልና።
አትውጣ ተብሎ ሁሉ ከቤት ቀርቶ፣
ሰው ከሰው እንዳይቀርብ ደጃፉ ተዘግቶ፣
በዘር ተከፋፍለን በቋንቋ ተጣልተን፣
ከአንድነት ከፍቅር ልዩነትን መርጠን፣
ዓለም ግራ ገብቶት ስትጨነቅ ምድር፣
ዙሪያዋን ሲከባት መልስ የሌለው ችግር፣
ሰው ወዳድ አክባሪው የእኔ አባት ይረፉ፣
የዓለምን ትርምስምስ ሳያዩ አንቀላፉ።
እምነቴ ሙሉ ነው የለኝም ጥርጥር፣
በማይቀረው ተድላ በትንሣኤው ክብር፣
የታመነ ቃል ነው አባቴን አያለሁ፣
ሁሉ በክርስቶስ እንዲቻል አውቃለሁ።
አባቴ መንገዶት መምጫዬ ነውና
አይርሱኝ በጸሎት በቤቱ እንድጸና
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
መልአከ ገነት ቀሲስ በለጠ ይረፉ
ሚያዝያ 23. 2012. ዓ/ም
በእግዚአብሔር ይዳኛል !!ስለዚህ ደሃ ተበደለ ፍርድ ተጓደለ ብሎ መፍትሔ ለማበጀት ተፈጥራለሁ። ስለዚህ ወገኖች በተለይ መሪ የሆንን ሰዎች ለተቸገሩት መፍትሔ ላጡት በእግዚአብሔር ቃል ላይ ቆመን ምድራዊ ጥያቄዎቻቸውን መመለስ እውነትን መግለጥ የልባቸውን ጥያቄ መመለስ እንድንችል ፈጣሪ ማስተዋል ይስጠን #ማስተዋል_ይብዛልን ።
" በሰማርያ ተራራ የምትኖሩ፥ ድሆችንም የምትበድሉ፥ ችጋረኞችንም የምታሰጨንቁ፥ ጌቶቻቸውንም። አምጡ እንጠጣ የምትሉ እናንተ የባሳን ላሞች ሆይ፥ ይህን ቃል ስሙ። "እኔ የእስራኤል ቅዱስ አምላክ ነኝ !! ህዝቤን አጽናኑ