Рет қаралды 5,687
በአለማችን የሚገኙ ሰፋፊ የውሃ አካላት መጠናቸው እየጨመረ በመጣበት በዚህ ወቀት የስነምድር ተመራማሪዎች አዲስ ውቅያኖስ በአፍሪካ ምድር ሊፈጠር ይችላል የሚል ውይይትና ምርምርን ማድረግ ጀምረዋል፡፡ ውስብስብ የሆነ ገፅታ ያለው የአፍሪካ አህጉር አሁን ላይ የምድራችንን አቀማመጥ ይቀይራል የተባለውን ክስተት በዋናነት ስተናግዳል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡ በአፍሪካ አህጉር በቀንዱ አከባቢ ደግሞ የአፋር ትሪያንግል ይገኛል፡፡ ይሕ ስፍራ የኑቢያ ሶማሊያ እና አረብ አምባዎች ወይም በእንጊሊዘኛው ፕላቱዎች የሚሰናሰኑበት convergence ነው፡፡ ውስብስብ የሆነ የስነምድር ገፅታ ያለው የአፋር ትሪያንግል ነው እንግዲህ ይህን በንጠት ምክንያት ይከሰታል የተባለውን የስነምድር ለውጥ ሊያስተናግድ ይችላል እየተባለ ያለው፡፡
የዊዎን መረጃ እንደሚያሳየው ከአውሮፓውያኑ 2005 ወዲህ የአለማችን ትኩረት በዚህ አከባቢ ስላለው ነገር ሆኗል፡፡ በኢትዮጵያ አፋር ክልል ፡፡ በአፋር በረሃ ፡፡ መረጃው እንደሚለው በዚህ አከባቢው ፈጣን ያልሆነ ነገር ግን የአፍሪካን አህጉር የሚከፍል የምድር ውስታዊ እንቅስቃሴ እየተስተዋለ ነው፡፡ በ2005 የአውሮፓውያኑ አቆጣጠር 35 ማይል ገደማ የሚረዝም የመሬት መሰንጠቅ ወይም መተርተር በዚህ የኢትዮጵያ በረሃማ አከባቢ ተፈጥሯል፡፡ እንደዚህ አይነት ሁኔታዎች ደግሞ ከመሬት የውስጠኛው ክፍል ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ መኖሩን የሚያሳዩ ናቸው፡፡
የስነ ምድር ተመራማሪዎችን ጠቅሰው የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት በሚቀጥሉት ከ አምስት እስከ 10 ሚሊዮን ባሉ አመታት ውስጥ አፍሪካ ለሁለት ትከፈላለች፡፡ ይህም አዲስ ውቅያኖስ በምድራችን እንዲፈጠር እድልን ያመቻቻል፡፡
#ኢትዮጵያ #አዲስአበባ #ሰበርዜና #አፋር