Рет қаралды 4,736
የየካቲት 01 ቀን 2017 የዓለም ዜና
• በምሥራቃዊ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የሚንቀሳቀሱ ሁሉም ታጣቂ ቡድኖች በአፋጣኝ ግጭት እንዲያቆሙ የኬንያው ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ ጥሪ አቀረቡ።
• የሱዳን ጦር በሰሜናዊ ኻርቱም የሚገኘውን ካፎሪ ወይም ባሕሪ የተባለ ቁልፍ አካባቢ መልሶ መቆጣጠሩን አስታወቀ።
• በሰሜናዊ ማሊ በሀገሪቱ ጦር እና የሩሲያው ቫግነር ቅጥረኛ ወታደሮች አጀብ በመጓዝ ላይ በነበረ የተሽከርካሪዎች ቅፍለት ላይ በተፈጸመ ጥቃት 32 ሰዎች መገደላቸውን ባለሥልጣናት ዛሬ ቅዳሜ ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ተናገሩ።
• ሐማስ ሦስት ታጋቾችን፤ እስራኤል 183 ፍልስጤማውያንን በቀይ መስቀል በኩል ለቀቁ
• ዩክሬን በሩሲያ ኩርስክ ግዛት አዲስ ጥቃት መጀመሯን ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ አረጋገጡ።
• ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ቱሩዶ አዲሱ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ካናዳን ወደ አሜሪካ ለመጠቅለል ያቀረቡት ሐሳብ ተጨባጭ እንደሆነ አስጠነቀቁ።