Рет қаралды 6,306
የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ (ESFNA) ዘንድሮ በሚያደርገው የ41ኛው አመታዊ የእግር ኳስ ውድድርና ባህላዊ ዝግጅት በአትላንታ-ጆርጂያ ከተማን ይካሄዳል::
"ኢትዮጵያዊነት ይቅደም! " በሚል ኢትዮያዊነት ስሜት የተጋጀው የዘንድሮው ውድድር ከሌሎች አመታት ለየት ባለ ሁኔታ ለመጀመሪያ ጊዜ ለስምንት ቀናት ይሆናል።
አንድ ተጨማሪ ቀን የተጨመረው የእግር ኳስ ውድድሮችንና በውድድሩ ወቅት የሌሎች ዝግጅቶችን የጊዜ ጥበትን ለመቀነስ ነው፣ ሲል ፌዴሬሽኑ አስታውቋል።
ስለሆነም፣ የዚህ አመት ዝግጅት ከቅዳሜ June 29 እስከ ቅዳሜ July 6, 2024 ይሆናል።
ከተለያዩ የአሜሪካ፣ ካናዳና ከተለያዩ የአለም ክፍሎች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሚሰባሰበት ይህ ውድድር የእግርኳስና የተለያዩ ባህላዊ ዝግጆቶች ይካሄዱበታል። ከሁሉ ከሁሉ ግን አርብ ምሽት የሚደረገው የኢትዮጵያን ቀን ዝግጅት ግን ፣ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ሀገሩን እያሰበ የሚዘምርበት፣ የሀገሩን ፍቅር ከሩቅ ሆኖ የሚያስታውስበት የባህላዊ ዝግጅት ቀን ነው።
ሌላው ሳምንቱ ቆይታ ጊዜ የሚደረጉት የእግርኳስ ውድድሮች ፣ በስፍራው የተገኘውን ህዝብ ልብ እየሰቀለ ይከርምና ወደአንዱ ከተማ ዋንጫዋ ትጓዛለች። ዘንድሮስ ወዴት ትሄድ ይሆን?
በውድድሩ ተካፋይ ከሆኑት ከተሞች እግርኳስ ቡድኖች ውስጥ በዋንሽንግተን-ሲያትል የሚገኙት የባሮና የዳሽን እግርኳስ ቡድኖች ይገኙበታል። እነዚህ ቡድኖች በESFNA ውድድር ጠንካራ ከሚባሉት ቡድኖች ውስጥ ይመደባሉ። የዘንድሮው ዝግጅታቸውን በተመለከተ ምን ይላሉ?
⚽ መርካቶ ስፖርት ⚽
💚💚💛💛❤️❤️