Рет қаралды 11,957
በአዋሳ ቅ/ሰበካ የመሃል አዋሳ ንዑስ ሰበካ መዘምራን ከሐምሌ 09-11/2013 በአዋሳ እናት አጥቢያ በተዘጋጀ ጉባዔ የቀረበ መዝሙር
ግጥም/Lyrics
ለዕንቆቅልሼ መጥቼ ለጥያቄዎቼ መልስ
ጥበብህ አስደንቆኛል እስከማይቀርልኝ ነፍስ
ከነገሩኝ ከሰማሁት ከአየሁት እጅግ ይበልጣል
ኢየሱስ ከሁሉ በላይ ነህ ፍቅርህ ልቤን ማርኮታል
1. ብዙ ነበረ በልቤ ያለው ማጫውትህ
እንድትፈታልኝ የምፈልገው የምለምንህ
ግን ፊትህ ስቆም መልካምነትህን ሳስተውለው
ዕንቆቅልሼን ችግሬን ሁሉ ያኔ ረሳሁ
ፍቅር ነው ሲገለጥ ማንነትህ
ሲፈለግ በጸሎት ምልጃ ፊትህ
ያስረሳል የሚናወጠውን ሁሉ
ምቾት ነው ኢየሱስ ከአንተ ጋር መዋሉ
2. ከሽቱ በላይ ከከበረ ዕንቁ አስበልጬ
በልቤ ከአለው ከመልካም ነገር ሁሉ መርጬ
የነፍሴን መስዋዕት መርቼ ሰዋልሃለሁ
በየማለዳው ስምህን ዘውትር እባርካለሁ
ፈታኸው ስውር ነገሬን ኢየሱስ
ሽቶዬ ምስጋናዬ ለአንተ ይፍሰስ
በፍጹም አሳቤ ወድጄሃለሁ
ዘለዓለም በፍቅርህ እገዛልሃለሁ
3. በፊትህ ቆመው ከሚያገለግሉ ጋር
ዕድል አግኝቼ ምስጉን ተብዬ እንድቆጠር
ከዕርስትህ ወገን ከቅዱስ ሕዝብ ለቀላቀልከኝ
የማልሰስተው በልቤ የሞላ ምስጋና አለኝ
ውሰደው የእኔ የምለውን ነገር
በሕይወቴ በዘመኔ ሁሉ ክበር
ፍቅር ነህ አሁንም እቀርብሃለሁ
በፍጹም ኃይሌ ዘምርልሃለሁ
የአፌን ነገር የሰማኸኝ
ከመልካምነት ያጠገብኸኝ
ስለውለታህ ምን መልሳለሁ
በምስጋናዬ አከብርሃለሁ
በምስጋናዬ አከብርሃለሁ
በዝማሬዬ አነግስሃለሁ
በእልልታዬ አከብርሃለሁ
ስለውለታህ ምን መልሳለሁ