Рет қаралды 42,941
ትንቢተ ኢሳይያስ 51:3
እግዚአብሔርም ጽዮንን...ምድረ በዳዋንም እንደ ዔደን በረሀዋንም እንደ እግዚአብሔር ገነት ያደርጋል፤ ደስታና ተድላ ምስጋናና የዝማሬ ድምፅ ይገኝበታል::
አለልኝ!
አለልኝ ኢየሱስ የምታመነው
ሳይሰጋ ልቤ የሚያምነው
ቃሉን ነው ስሙን ነው የምተማመነው
እልሰጋም መንገዴ እውነት ነው
እኖራለሁ በእምነት በኪዳኑ ረድዔት
ሕይወቴ ሆኖ ጌታ አለ የኔ ቤት
እኖራለሁ በእምነት በኪዳኑ ረድዔት
በረከት ሆኖ ጌታ አለ የኔ ቤት
አለልኝ ኢየሱስ:አለልኝ ንጉሱ
'' በሙላት '' መንፈሱ
ቤቴል የእግዚአብሔር ቤት የአማኞች መንደር
ዘሬ እህል ፍለጋ አይለቅም ሀገር
ፃድቅ እንደ አንበሳ አይፈራ አይቸገር
ይሰጣል ይዘራል እንጂ አይበደር
አለልኝ ኢየሱስ:አለልኝ ንጉሱ
'' በሙላት '' መንፈሱ
የዘላለም አምላኬን መኖሪያዬ አድርጌ
ፅድቅና መንግሥቱን አስቀድሜ ፈልጌ
ይከታተለኛል በረከት ተግቶ
ምድር እንዴት ትሰስት ሰማይ ተከፍቶ
እኖራለሁ በረሃው ዔደን:እኖራለሁ ገነት ሆኖልኝ
'' ከዓለቱ ውሃ " ምንጭ ፈልቆልኝ
ተማምኘው አንዳች ነገር
" ሳልቸገር
እኔን/2x የያዘኝ እጁ ነው/ጌታ ነው
" የሚያኖረኝ ቃሉ ነው/ኪዳን ነው
ዘዳ 33:27-28/ማቴ 6:24-34/1ቆሮ 10:1-4/ኢሳ 51:3/ዘዳ 8:1-10/መዝ 23:1-6