Рет қаралды 7,232
ከነሐሴ 06-08/2014 ድረስ በሀዋሳ እናት አጥቢያ በተካሄደው የሀዋሳ ቅ/ሰበካ ዓመታዊ የወጣቶች ጉባዔ ላይ የቀረበ ዝማሬ።
ግጥም/Lyrics
እመን በእግዚአብሔር በኩራት አትናገር
እርሱ አዋቂ ነው ነገርህ በእጁ ነው
ስታይ ዙርያው ቢጨላልም
ሁኔታዎች ቢያስፈራሩ
የአንተ ነገር ይገድደዋ
ከተፍ ይልልሃል
1. እስራኤልን እየመራ
በአስጨናቂው በዚያ ስፍራ
ማዕበል ወጀብ ሲያስፈራቸው
በድል ነበር የመራቸው
ያ ኢየሱስ ዛሬም አለ
ያንን ባሕር የከፈለ
ከፊት ሆኖ ይመራሃል
እመን እንጂ ያሳይሃል
በል ከእንግዲህ አትፍራ
ጌታ አለ ከአንተ ጋራ
ሠልፉ የእግዚአብሔር ነው
ድሉ ደግሞ የአንተ ነው
2. በምትሰማው በምታየው
ከቶ አትደንግጥ በሚሆነው
የዓለም ፍጻሜ መጨረሻው ነው
ሚሆነው ሁሉ ምልክቱ ነው
ባይሆን ንቃና አምላክህን ጠብቀው
መቅረዝህንም እስቲ ተመልከተው
ጎድሎ ከሆነ እዚሁ መቅረትህ ነው
ኢየሱስ ሊመጣ ይኸው በደጅህ ነው
* *
መኖርያዬ የዘለዓለም አምላክ ነው
ከበታቹ ተማምኜ ኖራለሁ
ደረቁ እንኳ በርሱ እንደሚለመልም አውቃለሁ
ሁሉ የእርሱ ሆኖ በኢየሱስ ታምኛለሁ
ለምን እፈራለሁ
ለምን ለምን ለምን እፈራለሁ
ለምን ለምን ለምን እሰጋለሁ
የሱስን ይዣለሁ/ በኢየሱስ ታምኛለሁ