Рет қаралды 1,708
የመጀመርያዋ የአጅሪት ፖድካስት ቆይታችን ላይ ስለ ሴትነት እና ውሳኔ ሰጭነት፣ ፆታ ላይ የተመሰረተ የተዛባ የቤት ውስጥ የስራ ጫና እና ተፅዕኖ፣ ብሎም ማህበረሰቡ ለሴቶች እና ለወንዶች የሚሰጠውን የተለያየ ቦታ እና ክብር ከሶስት ጓደኛሞች ጋር የምናደርገው ቆይታ ይሆናል። በርዕሳችን ላይ ወይም በተወያየንባቸው ጉዳዮች ዙርያ ማንኛውንም አይነት ጥያቄ ወይንም አስተያየት ካላችሁ ከስር ፃፉልን፣ ለመመለስ ዝግጁ ነን!
በዚህ ክፍል 51ኛ ደቂቃ ላይ ከተጠቀሱ ቁጥሮች መሃል፣ በአማራ ክልል በግጭት ወቅት ጥቃት የደርሰባቸውን ሴቶች በተመለከተ: የአማራ ክልል ሴቶች ማኀበር ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ሁሉአየሽ አወቀ፣ 4 ሺህ ሴቶች ተደፍረዋል የሚለውን የካቲት 20 ቀን 2016 ዓ/ም በማህበሩ ተወካይ የተደረገ ገለፃ ጠቅሰው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል መረጃው ያልተረጋገጠ እንደሆነ እና አክለውም፣ “ቁጥሩ ከዚህ በላይ ሊሆንም ይችላል፣ ሊያንስም ይችላል፣ ስትሰበስበው ነው የምታገኘው ” ሲሉ ለቲክቫህ እንዳስረዱ ለተመልካቾች ማሳሰብ እንፈልጋለን።