Рет қаралды 11,524
ኢትዮጵያ ለዘመናት አምጣ ከወለደችው አባይ ወንዝ በረከቱን ከመቋደስ ይልቅ አሻግራ በመስደድ ውለታዋን ዘንግተው መውጋት የሚዳዳቸው ሃገራትን ስታበለጽግ ቆይታለች፡፡ ይህ ዘመን ግን ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ላይመለሰ አክትሟል፡፡ይህ ጉዳይ የአባይ ግድብ መጠናቀቅ ብቻ አይደለም፡፡ይህ ቀን በወደፊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በታላቅ የሚዘከር ሁነት የተመዘገበባት - ዕለተ ዕሁድ ጥቅምት 2 ቀን፣ 2017 ዓመተ ምህረት የዓባይ ናይል ውሃ የግብፅ የብቻ ንብረትነቱ ያከተመበት ቀን ኢትዮጵያ ልጇን በህግ የመለሰችበት እጅግ የተከበረ ትልቅ ቀን ነው። ኢትዮጵያን ተጠቃሚ የሚያደርገው ሰነድ በ 6 የተፋሰሱ ሀገራት ተፈርሞ፤ ወደ አፍሪካ ህብረት እንዲደርስ ተደርጎ፤ እነሆ በህብረቱ ህጋዊ ተቋም ይመሰረትለት ዘንድ ጣጣውን ጨርሶ በዛሬው ዕለት ስኬቱ ተበስሯል።
✔️Subscribe here: www.youtube.com...