Рет қаралды 12,873
የ1ኛ ሳሙኤል የመጨረሻው ክፍል በመሠረቱ በሳኦልና በዳዊት መካከል ያለውን ግጭት የሚተነትን ክፍል ነው። ዳዊት ንጉሥ እንዲሆን በእግዚአብሔር ተመርጦ ነበር። በእግዚአብሔር ዓይን የእግዚአብሔር ሕዝብ ትክክለኛ ንጉሥ ዳዊት ነበር፤ ነገር ግን ዳዊት በበርካታ ዓመታት ኮብላይ (ተሳዳጅ) ሆኖ በዋሻ ተደብቆ ኖረ። ከሳኦል የግድያ ሙከራ ለማምለጥ ከቦታ ወደ ቦታ ይዘዋወር ነበር። ንጉሥ ለመሆን ምንም ዓይነት ኃይልን ለመጠቀም ፈቃደኛ ሳይሆን ቀረ። ጥላቻና ብቀላ ወደ ሕይወቱ እንዲገባ አልፈቀደም። ይልቁንም እግዚአብሔር ራሱ በሳኦል ላይ እስኪፈርድና መንግሥቱን እስኪሰጠው ድረስ ለመጠበቅ ወሰነ። ይህ ለእኛ ብርቱ ማስጠንቀቂያ ሊሆነን ይገባል። ነገሮችን በራሳችን እጅ በማከናወን የጎበጠውን ለማቃናት ከመፍጨርጨር ይልቅ እግዚአብሔርን በትዕግሥት ልንጠብቀው ይገባል። በተጨማሪ ከእግዚአብሔር ጋር በፍጹም ታዛዥነት በምንኖርበት ጊዜ እንኳ በብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ማለፍ እንደምንችል ያስተምረናል።
በተጨማሪ እዚህ በተከታታይ ትምህርት ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት
- https: //www.operationezra.com
• www.operationezra.com ...
• www.operationezra.com ...
© Operation Ezra Bible College