Рет қаралды 11,333
ኢዩኤል፦
በኢዩኤል ዘመን እግዚአብሔር ታላቅ የአንበጣ መንጋ መቅሠፍት በእስራኤል ላይ አፈሰሰ። የምድሪቱ ሰብል ጠፋ። እንስሳት የሚግጡትን ሣር አጡ። ኢዩኤል ይህ የእግዚአብሔር ፍርድ መሆኑን ያውቅ ነበር። ስለዚህ የእግዚአብሔር ሕዝብ በንስሐ በመመለስ፥ በመታዘዝና በመቀደስ እንዲኖሩ ይለምናል።
አብድዩ፦
ከብሉይ ኪዳን መጻሕፍት መካከል ትንሹ አብድዩ ነው። ትንቢተ አብድዩ አንድ ምዕራፍ ብቻ ያለው ሆኖ ስለ ኤዶምና ከእግዚአብሔር ዘንድ ስለሚመጣባት ፍርድ ይናገራል። በአሕዛብ መንግሥታት ላይ ከሚያተኩሩ ሦስት የትንቢት መጻሕፍት መካከል አንዱ አብድዩ ነው።
ለሌላ ተጨማሪ ትምህርቶች፦
- https: //www.operationezra.com
• www.operationezra.com ...
• www.operationezra.com ...
© Operation Ezra Bible College