Рет қаралды 30,302
#የመዝሙሩ_ግጥም
በሀዘኔ በጭንቀቴ
መፅናኛዬ ነሽ እረዳቴ
አመአምላክ አደራ ድንግል እመቤቴ
አመአምላክ አደራ ድንግል እመቤቴ
በሀዘኔ በጭንቀቴ
መፅናኛዬ ነሽ እረዳቴ
አመአምላክ አደራ ድንግል እመቤቴ
አመአምላክ አደራ ድንግል እመቤቴ
አለም ትለኛለች ተስፋቢስ ብቸኛ
ሳለቅስ ሳነባ አይታኛለችና
ከቤተመቅደሱ እኔስ እናት አለኝ
በሀዘኔ ሰአት አለሁ የምትለኝ
ውበት ነሽ ለቤቴ ለኑሮዬ ፋና
ውበት ነሽ ለቤቴ ለኑሮዬ ፋና
ድንግል ሆይ አትለይኝ ብቻዬን ነኝና
ድንግል ሆይ አትለይኝ ብቻዬን ነኝና
አይቀርም መፈተን መከራን መቅመሱ
ለዚህ አለም ጣጣ መተከዝ ማልቀሱ
አምናለሁ እናቴ እንደምታዝኚልኝ
ሰው ሁሉ ሲሸሸኝ እንደማትለይኝ
አትለይኝ ማንም የለኝ
ከጎኔ ቁሚ ብቻዬን ነኝ
አትለይኝ ማንም የለኝ
ከጎኔ ቁሚ ብቻዬን ነኝ
እሾህ አሜኬላ ቋያ ነው መንገዱ
ቁሚልኝ እናቴ የልጅሽ ነው ፍርዱ
አንዴ ሲሞላልኝ ደግሞ ሲጎድልብኝ
ወደአንቺ አሮጣለሁ እንድታባብይኝ
አክሊሌ ነሽ ማርያም ሞገሴ ነሽ
አክሊሌ ነሽ
አክሊሌ ነሽ ማርያም ሞገሴ ነሽ
ለአለም ሞኝነት ነው በስምሽ ማመኑ
ታምርሽን መስማቱ ውዳሴ መድገሙ
እኔስ ምስክር ነኝ ዛሬም ለዘለአለም
ማርያምን ሳይጠሩ ከቶ መፅደቅ የለም
ድንግል እናቴ ነይ ድረሽልኝ
ወገን የለኝም ቀርቦ የሚያፅናናኝ
ከአጠገቤ ሁኚ እና አለሁ በይኝ
ይቆይልኛል ያልኩት ከእጄ ላይ አልቆ
በሀዘን በሰቆቃ ጉልበቴ ደቆ
በረከት አልባ ሆኜ እንዳልከፋ
ድረሽልኝ እናቴ ነይ የኔ ተስፋ
ድንግል እናቴ ነይ ድረሽልኝ
ወገን የለኝም ቀርቦ የሚያፅናናኝ
ከአጠገቤ ሁኚ እና አለሁ በይኝ
ዚቅ ሚድያ ZIQ MEDIA