Рет қаралды 16,406
ያዕቆብ ይህንን መልዕክት በመጻፍ አማኞችን ሊያሳስብ የሚፈልገው አማኞች በክርስቶስ ኢየሱስ ያላቸውን እምነት በሥራ ማሳየት እንዳለባቸው ለማስታወቅ ነው። በርግጥም ሰው የሚድነው በሥራ ባይሆንም፣ እውነተኛ እምነት ግን በሥራ ይታያል። በመሰረቱ ሐዋሪያው ጳውሎስ እንዳስተማረው፣ አማኝ በእምነት የሚድንበት አንደኛው ምክንያት “መልካሙን ሥራ” ለማድረግ ነው (ኤፌ 2፡8-10)። ሆኖም ግን ሰው በክርስቶስ አምናለሁ ካለ የማመኑ አይነተኛ ምልክት በእምነቱ ምክንያት የሚያፈራው መልካሙ ሥራው ነው። ይህንን እውነት ለማስጨበጥ ያዕቆብ የተለያዩ የሕይወት ገጽታዎችን እያነሳ፣ በእያንዳንዱ የሕይወት ገጽታ ውስጥ አማኝ እንደ ክርስቲያን እንዴት መኖር እንዳለበት ያሳስባል።