Рет қаралды 200,744
በእንደዚህ አይነት እና በተለያዩ ምክንያት በመናፍስት ተይዘው የሚሰቃዩ አሉና ሁላችሁም አይተን ላላዩትም አሳይተን የዲያብሎስን አሰራር እና ስልት እናጋልጥ
እግዚአብሔርን በአፍ አመልካለሁ ብለን በተግባር ስንከዳው፤ በአንጻሩ ሰይጣንን በአፍ ከድቻለሁ ብለን በተግባር አብረነው ስንኖር፤ "እኔ መንፈስ የለብኝም" እያልን በ'የለብኝም" ድምፅ ይበልጥ እንደሌለ ሆኖ የሚቀመጥበትን ጊዜ እያረዘምንለት፤ በኛ ባሕሪይ ውስጥ ምሽግ ሰርቶ የሚያደፍጥበትን አቅም እያሳደግንለት፤ የክፉ መንፈስ መግለጫ የሆነውን ኃጢአት ግን እንደልብ እየሠራን በእግዚአብሔር ነገራት ላይ ድንዝዝ ብለን ስንቀመጥ፤ "ምንድነው ነገሩ? ለምንድነው በእምነቴ ውስጥ በእውነተኛ ምግባር መመላለስ ያቃተኝ? እውነት ከመንፈስ የጸዳሁ ሰው ብሆን ኖሮ ኑሮዬስ ከጥፋት ገጽታዎችና የኩነኔ ተግባራት ለምን ጸድቶ አይታይም? ኃጢአትን ያለማቋረጥ እየሠራው የኃጢአት ኃይል የሆነው የዲያቢሎስ መንፈስ የለብኝም ማለት እንዴት ይስማማል?" ብለን አንመረምርም፡፡
ዓለማችን በተለይ በዚህ ዳፍንታም ዘመኗ፤ ዓለም ላይ ገዢ ሆኖ በእያንዳንዱ የሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ የጥፋትና የማጥፋት መሪ ሆኖ የተቀመጠው ጠላት ላይ የመንቃትን እውነት ፈጽማ አውጥታ፤ ይልቁኑ ኃጢአትን ለምዳና የሕይወት አንድ ጉዳይ አድርጋ ከጊዜያት ግስጋሴ ጋር በሚጨምር የእርግማን፣ የርኩሰትና የክፋት ገጽታዎች የተሞላች ስትሆን ጊዜ ጽድቅ ኃጢአት፥ ኃጢአት ደግሞ ጽድቅ ሆኖ ተገልብጦ ቁጭ አለ፡፡
ሰዎችም ታዲያ በዘመናት መካከል ስንመላለስ፤ የቅድስና እውነታዎችን እንደ ባርነት እንድንቆጥር በሥጋ ምቾት ውስጥ የተደበቁት ኃጢአቶች የዕለት ክስተቶቻችን ሆነው እንዲላመዱን፤ በጽድቅ አምባዎች ላይ መቆም በዓለም ውስጥ የሚገባንን ኑሮ እንዳንኖር የተገዢነት ቀንበር የሚያሳርፍ ተጽዕኖ እንዳለው ክፉ መናፍስቶች በቀላልና በሚስማማን የስልት ጥበብ ሲያሳምኑን፤ የፉክክር ትልቅ መድረክ ሆና በተቀረጸቺው የርዮተ ዓለም አካሄድ ውስጥ አሸናፊ ለመሆን የርኩሰትንና የኃጢአትን ግብራት መፈጸም አስፈላጊ እንደሆነ በጋራ ስምምነት ተወስዶ፤ "ኃጢአት የማይሠራ ሰው የለም" እያልን እርግማንን በነጻ እያስተዋወቅን፣ ግፍን በነጻ እያጸደቅን፣ ርኩሰትን በነጻ እያስፋፋን፤ "ሁሉም ሰው ኃጢአት ይሠራልና እኔም በዚህ ሁሉነት ውስጥ የደርሻዬን ኃጢአት ልውሰድ" የሚል የየግል ሕይወትን እየመራን፤ የከሳሻችንን ዲያቢሎስ የኃጢአት መዝገብ እያሳደግንለት የነፍሳችንን ጩኸት አፍነን የሥጋችንን ሹክሹክታ እየሰማን ዝም ብለን ቀን እንቆጥራለን፡፡