Рет қаралды 85
#Apostolic_church_songs #Gerji_Amen_Choir #Apostolic_songs_with_lyrics
በገና ደርዳሪው ቅኔን ቢደረድር
ተናጋሪው ሁሉ/ውለታህ ያለበት ስለአንተ ቢናገር
ምን ቃላት ይገልጽሃል ኢየሱስ
የቱ ቃል ይገልጽሃል አንተን
1) ትውልድ በትውልድ ሲተካ ሲቀየር
የሁሉን ከንቱነት ሰባኪው ሲናገር
አንተ ግን አንተ ነህ የፍጥረታት ንጉስ
በቀረቡህ ቁጥር ሁልግዜ አዲስ
ተባረክ አሜን ልበልህ እኔ
የነፍሴን ዜማ የልቤን ቅኔ
ባየሁህ መጠን በገባኝ ልክ
እየፈራሁህ (እየተገዛሁ) የሱስ ላምልክህ
2) በክብርህ ሰማይን የሞላህ ምድርን
ልብና ሀሳብን የምትመረምር
የሰው ልጅ አይምሮ የማይደርስብህ
ሁሉንም የምትችል ስምህ ኤልሻዳይ
በገና ደርዳሪው...
3) ፍጥረት ይበረታል ተስፋ አድርጎ አንተን ሲያይ
የተቆረጠውን ያበቃውን ቀጣይ
ሕይወት ዘርተህበት የሞተን ነገር
ሰላም ይሁን የምትል በተዘጋ በር
ተባረክ አሜን ...