Рет қаралды 28,245
በሰዎች መካከል የሚካሄድ መልካም ጦርነት ወይም ገድል የለም። ሰዎች እርስ በርስ እንዲዋደዱና እንዲደጋገፉ እንጂ እንዲጋደሉ ስላልተፈጠሩ። እግዚአብሔር በሰዎች መካከል ፍቅር እንጂ ጠላትነትን አላኖረም። ነገር ግን እግዚአብሔር መልካም የሚለው፣ ቅዱስ የሚለው ጦርነት አለ። ይኸውም በሰው ልጅና በዲያቢሎስ መካከል ያለ ጦርነት ነው። ይህንን ጠላትነት ያኖረው ራሱ እግዚአብሔር ነው። ታዲያ ይህንን መልካም ገድል ምን ያህል እየተጋደልን ነው? ይህንን ቅዱስ ጦርነት ምን ያህል በድል እየመራን ነው? የቃሉ መምህር ወንጌላዊ ያሬድ ጥላሁን በኤፌ. 6፥15 ላይ መሠረት በማድረግ በሁለቱ ጦርነቶች መካከል ያለውን ልዩነትና መልካሙን ገድል እንዴት መጋደል እንዳለብን በጥልቀትና በስፋት ይነግረናል። የሰላም ወንጌል ምንድነው? ለምን በወታደር ጫማ ተመሰለ? ወታደራዊ ቅድመ ዝግጅት ስንል ምን ማለታችን ነው? ይህን ቪዲዮ በትጋት እስከ መጨረሻው ይከታተሉ። ሰብስክራይብ፣ ላይክ እና ሼር ማድረጎትን አይርሱ።