Рет қаралды 154,611
ወዳጆቼ ሉቃስ ምዕራፍ 7:36 ላይ ያለችው ሀጢአተኛ ሴት ትዝ ትላችኋለች? ይህቺ ሴት በከተማው የታወቀች ሀጢያተኛ ነበረች እና አንድ ቀን ኢየሱስ ወደ አንድ ፈሪሳዊ ቤት ለምሳ እንደተጋበዘ ስትሰማ ሽቱዋን ይዛ ወደ ፈሪሳዊው ቤት ዘው ብላ ገባችና እዬዬ እያለች ኢየሱስ እግር ስር ሽቶዋን ሰበረች ፤ ይህቺ ሀጢያተኛ ምናልባት ይሄ ፈሪሳዊ ቤት ኢየሱስ በሌለበት ገብታ ቢሆን ኖሮ ትወገር ወይ ደግሞ የሆነ ነገር ትደረግ ነበር። እኛም ልክ እንደዚህ ነን ኢየሱስ ከሌለን እርቃን እንቀራለን ያገኘን ሁሉ ይገድለናል ። ያለ ኢየሱስ ሁሉም ነገር ለኛ ጠላት ነው ፣ ወደ አብ ፊትም መቅረብ አንችልም ነበር እንሞታለን።
ያለ ኢየሱስ ፈሪ እንሁን ፣ በሌለህበት አንችልም እንበለው ፣ ያለ እረኝነትህ ያለ ጠረንህ ያማረ መስክም ይቅርብን እያልን ህልውናውን እንፈልግ። ለኛ እረኛ በሌለበት ውብ መስክ ላይ ብንሰማራ አውሬ ይበላናል ነገርግን እርሱ ባለበት ፣ ጠረኑ ባለበት ፣ ህልውናው ባለበት መስኩ እንኳን ባያምር ህይወት አለው። እንፈልገው.... እንጠማው
ተባረኩ ❤