Рет қаралды 1,033
ነቢዩ አሞጽ በስምንተኛው ክፍለ ዘመን ከይሁዳ ወደ እስራኤል የተላከ ነቢይ ነበር። መልእክቱ በዋነኛነት የፍርድ መልእክት ሲሆን ወደ መጨረሻ አከባቢ ከፍርድ በኋላ ስላለው ተስፋም ተናግሯል። ነቢዩ የሕዝቡን ሃይማኖታዊ ክህደት፣ ግብረ ገባዊ ውድቀት፣ ፖለቲካዊ ቀውስ፣ ወዘተ. በመግለጥ ፍርድ አይቀሬ መሆኑን ያስታውቃል። ባለጸጎች ይበልጥ እየበለጸጉ እና ድኾች ይበልጥ እየደኸዩ ይሄዱ ነበር። በማኅበረ ሰቡ መካከል ግፍ፣ ስስት፣ ኢፍትሐዊነት፣ በጥቅሉ የግብረ ገብ ችግር በሥፋት ነበረ። ጻዲቁን ሰው በገንዘብ፣ ድኻውን በጫማ መቀየር፣ አባትና ልጅ ከአንዲት ሴት ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈጸም፣ በራስ ወዳድነት ላይ ያተኮረ ቅንጦት፣ ወዘተ. በሕዝቡ መካከል ይስተዋል ነበር። ነቢዩ እውነተኛ አምልኮ ማኅበራዊ ፍትሕን እንደሚያሰፍን በመግለጥ እስራኤል እየመጣ ካለው ፍርድ እንደማታመልጥ ያስታውቃል። ዛሬም እግዚአብሔር ስለ ሰዎች፣ ስለ ማኅበራዊ ጉዳይ ግድ የሚለው አምላክ ነው። የመጽሐፉ ማእከላዊ ጉዳይ ማኅበራዊ ፍትሕ ነው። ይህቺን አጭር ቪድዮ በመመልከት የአሞጽን ትኩረት መረዳት ይቻላል።