Рет қаралды 19,664
ዘካርያስ
ከነቢዩ ሐጌ በኋላ ሁለት ወር ዘግይቶ አገልግሎቱን የጀመረው ነቢዩ ዘካርያስ ተገቢና ትክክለኛ በሆነ አምልኮ አስፈላጊነት ላይ ያተኩራል። ዘካርያስ ንስሐ እንዲገቡና መንፈሳዊ ተሐድሶ እንዲኖራቸው ለሕዝቡ ጥሪ አደረገ፡፡ የእግዚአብሔር ሕዝብ በንጹሕ ልብና እግዚአብሔርን ለማምለክ በሚፈልግ ዝንባሌ ወደ እግዚአብሔር በሚቀርብበት ጊዜ ከሁሉም የበለጠ ለአምልኮ የሚያስፈልገውን ነገር አሟልተዋል ማለት ነው። አምልኮ የሚፈልገው ሕንጻን ሳይሆን በሚገባ የተዘጋ ልብን ነው፡፡ ስለዚህ ዘካርያስ የቤተ መቅደሱ ሥራ በሚጠናቀቅበት ጊዜ ሕዝቡ እግዚአብሔርን በሚገባ እንዲያመልኩ በቅድሚያ የሕዝቡን ልብ ለማዘጋጀት ጥሯል።
ሚልኪያስ
የመጨረሻው የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ትንቢተ ሚልክያስ ስለ መሢሑ መምጣትና ከእርሱ በፊት ስለሚመጣው ኤልያስ የተስፋ ቃል በማስተላለፍ ይጠቃለላል። እግዚአብሔር ከሚልክያስ በኋላ አዳዲስ ትንቢቶቹን የሚናገሩ ነቢያት አልላከም። እነዚህም ዓመታት 400 የጸጥታ ዓመታት በመባል ይታወቃሉ።
ለሌላ ተጨማሪ ትምህርቶች፦
- https: //www.operationezra.com
• www.operationezra.com ...
• www.operationezra.com ...
© Operation Ezra Bible College