Рет қаралды 487
Josaphet Choir - Mulu Wongel Church
እሁድ ሚያዚያ 2 ቀን 2014 አ.ም በዋሽንግተን ሆቴል በነበረን የአጠቃላይ የእዮሳፍጥ እንደገና ፕሮግራም የእግዚአብሄርን እርዳታ እገዛ ፤የመንፈሱ መገኝት፤ በዝማሬ ፤በእግዚአብሄር ቃል፤ በጋሽ ደቤ(መጋቢ) አባታዊ ምክር፤ መረስረስ፤ መታተቅ እንደገና መታደስ ሆኖልናልና ይህንን ላደረገ ለሃያሉ ጌታ ለልዑል እግዚአብሄር ክብር ይሁን፡፡
ለዚህ ፕሮግራም መሳካት ሳታቋርጡ ስትጸልዩ ለነበራችሁ፤ ግዜያችሁን ለሰጣችሁን፤ ሃሳብ ላካፈላችሁን፤ በገንዘብ ለረዳችሁን፤ ሳውንድ ሲስተም ያለዋጋ የሰጣችሁን፤ ቪዲዮ ካሜራ ላዋሳችሁን፤ ሳውንድ ሲስተም ያመረ እንዲሆን ለተቆጣጠራችሁልን፤ በዝማሬ ላገለገላችሁን ለ22 እና ለአስኮ እኢዮሳፍጥ መዘምራን፤ አምልኮ በመምራት ላገለገላችሁን፤ በእግዚአብሄር ቃል፤ በድቁና ላገለገላችሁን፤ አዲሱን የእኢዮሳፍጥ የባንክ አካውንት እንድንከፍት ደግሞም ገንዘብ እንዲሰበሰብ ለረዳችሁን፤
በውጭ ያላችሁ በፕሮግራማችን ላይ ላይቭ የተከታተላችሁና ሰላምታ ያቀረባችሁ ሁሉ እንዲሁም ጥሪያችንን አክብራችሁ በሰአቱና የምሳ ውጭያችሁን በመሽፈን ለተገኛችሁና በሙሉ የመዘምራን ህብረት እግዚአብሄር ይባርካችሁ ተበረኩ፡፡
ጋሽ ደቤ እንደተናገረው ወደ መገኛችሁ ወደ ህብረታችሁ በመሄድ እንድታጠናክሩ አደራ እያልኩ ለሚቀጥለው ለሚኖረን ትልቅ የእግዚአብሄር ስራ ራሳችንን እናዘጋጅ ተባረኩ ያባቴ ብሩካን፡፡
ፍሬው ህይለማርያም
በአለም ዙሪያ የምትገኙ የቀድሞ ኢዮሳፍጥ መዘምራን አባላት ይህን መሰባሰብ መቀላቀል ትችላላችሁ።