Рет қаралды 21,664
ዝም አልልም አፌን አልዘጋ
ሳላመሰግን መሽቶ አይነጋ
እኔ ዝም ብል ድንጋይ ያመሰግን የለም ወይ
እጨምራለሁ ዛሬም ምስጋናን እልልታን በላይ በላይ
መቃብር ተከፍቶ የወጣሁ ነኝ ህይወት በእኔ ዘርቶ
የተፈቀደልኝ ከሰማይ እንድሆን ለእርስቱ ተካፋይ
ታዲያ ምንም እንዳላየ እንዳልተደረገለት
አይታዘብም ወይ ሰማይ ዝም ቢል የእኔ አንደበት
የተደረገልኝ እኔ ነፃ
የወጣሁኝ እኔ ከሞት
ያመለጥኩኝ እኔ
እንዴት ምስጋና/ እልልታ ያንሳል ከእኔ
ዝም ልል አልችልም ይዞኛል ውለታው ልቤ ገብቶ
መች እንዲህ በቀላል ይታለፋል የአምላኬ ደግነት ተዘንግቶ
ከንፈሮቼ በምሥጋና የሙሳ ቃል አወጡ
አጥንቶቼም በደስታ ለእርሱ ክብርን እየሰጡ
ምስጋና ምስጋና እላለሁ በፅዮን ፊቱ ቆሜ
በጠላት እራስ ላይ በዘይቱ ለቀባኝ ለሆነኝ ጉልበት አቅሜ
እጨምራለሁኝ እንጂ ምስጋናውን አላሳንስ
የእኔ ክብር ፊቱ ወርዶ ይገባል ሊልቅ ኢየሱስ
ማነው ከእኔ በቀር የታደለ ያገኘ ምህረት
አምላኩን በማወቅ የበረታ የኖረና የቆየ በህይወት
እኔ የተደረገልኝ የተቃናልኝ መንገዴ
ድንጋዮች ቀድመው ሳይጮሁ ላመስግነው በፈቃዴ
ሙሉ መዝሙር ለማግኘት የ Telegram ገፅ ይጠቀሙ
t.me/Apostolic_Church_TV_Radi...
#apostolicchurchofethiopia #apostolicsongs #lyrics #apostolicmezmur #samsonadefers