Рет қаралды 29,619
ከግንቦት 12-14 በአዲስ አበባ ሰበካ በጎፋ አጥቢያ በተደረገው ታላቅ ጉባዔ ላይ የቀረበ ድንቅ ዝማሬ።
ሰብስክራይብ በማድረግ ወንጌልን ለዓለም እናድርስ!
ግጥም/Lyrics
በገነነው ላይ ገንኖ በበረታው ላይ ብርቱ
የእርሱን ኃይል ተቋቁሞ ማን ይቆማል በፊቱ
ብፎክር ብመካበት አላፍርም በኢየሱስ
በሁሉ ላይ ጌታ ነው በሁሉ ላይ ንጉሥ
ስራውን ያዩ ኃይሉን የሚያውቁ
በምስጋናው ቃል ክብሩን ያድንቁ
እኔም አይቼ የእርሱን ችሎታ
እለዋለሁኝ ድንቅ የእኔ ጌታ
ድንቅ የእኔ ጌታ
* * *
አላደረገንም የጠላት ንክሻ
ምሕረቱ ሆኖልን ማምለጫ መሸሻ
እጁ በረታ እና በጠላታችን ላይ
አሻግሮ አቆመን ለክብሩ አደባባይ
ይዘመርለት ምሕረቱ
ይወራ ታላቅነቱ
የምድር ሁሉ ንጉሥ
ኃያል ነው የእኛ የሱስ
* * *
የድል ነሺ ድምፅ የድል የድል ምስጋና
በአደባባይ ላይ ይሰማ ከፍ ይበል እና
ያለ የነበር የሚኖር በቅድስናው
ኢየሱስ ይክበር ከፍ ይበል ዛሬም ምስጋናው
ከፍ ይበል ምስጋናው
ከፍ ይበል እልልታው
1. ሦስት አይበቃም አራትም ቢሆን ያንሳል
ካልደገምኸው ጠላትህ ወድቆ ይነሳል
ለማሸነፍ ከፈለግክ ጠላትህን
አታሳንስ አምልኮ ምስጋናህን
ሁለቴ ሦስቴ መትተህ አትተው
ፈራርሶ እስኪወድቅ ደጋግመህ ምታው
ድሉ የአንተ እስኪሆን ድረስ
ወደኋላ አትበል ስራውን ከማፍረስ
በምስጋና ድምፅ በአምልኮ
ይፈራርሳል ኢያሪኮ
በአምልኮ ጩኸት በምስጋና
ይወድቃል ግንቡ ገና ገና
ገና ገና ኢየሱስ ሲመለክ
ገና ገና ሲከብር እርሱ
ገና ገና በኢያሱ ላይ
ገና ገና ሲወርድ መንፈሱ
ገና ገና ትንሽ እንጎቻ
ገና ገና ብትሆንም እንኳን
ገና ገና ይፈራርሳል
ገና ገና የጠላት ድንኳን
ከፍ ይበል ምስጋናው
ከፍ ይበል እልልታው