Рет қаралды 21,025
መዝሙረ ዳዊት 117
ሃሌ ሉያ።
1 አሕዛብ ሁላችሁ፥ እግዚአብሔርን አመስግኑት፥ ወገኖችም ሁሉ ያመስግኑት፤
2 ምሕረቱ በእኛ ላይ ጸንታለችና፤ የእግዚአብሔርም እውነት ለዘላለም ትኖራለች። ሃሌ ሉያ።
ሃሌሉያ
ለክፋት የሆነው አለፈኝ
ለመልካም ልሆን ዘገየሁ
ከእኔ ይልቅ አወቅህልኝ
ካላየሁት ክፉ ተጠበቅሁ
ለምስጋና ተረፍሁ ለሃሌሉያ
ልትመሰገንብኝ ወሰንክልኝና
የተጠመደልኝ ሳይዘኝ አመለጥሁ
እንደ ምህረትህ ከጥፋቶቼ ዳንሁ
ሃሌሉያ /ብዙ ጊዜ
ያማረኝን ሁሉ ከመያዝ እጆቼ
በአንተ ተከለከሉ
ያፈቀርሁትን ወጥመድ ሳይገባኝ ሰበርህ
እያለቀስሁ አመለጥሁ
ለምስጋና ተረፍሁ ለሃሌሉያ
ልትመሰገንብኝ ወሰንክልኝና
የተጠመደልኝ ሳይዘኝ አመለጥሁ
እንደ ምህረትህ ኦ ...
ሃሌሉያ /ብዙ ጊዜ
የታሠርሁበትን ሰንሠለት በጠስህ
የትናንት አመፃዬን ታገስህ
ምን እላለው?!
አንደበት ደካማ ነው
እንዲያው ተመስገን!
ሃሌሉያ ...