Рет қаралды 27,812
መጽሐፈ ምሳሌ 15
16 እግዚአብሔርን ከመፍራት ጋር ያለ ጥቂት ነገር ሁከት ካለበት ከብዙ መዝገብ ይሻላል።
ጥቂቱ ይበቃል
በአመፅ ከተገኘ ግዝፈት
የፍቅር ትንሹ ይበልጣል
ከሃጢአተኛው መትረፍረፍ
የጻድቁ እጦት ይበቃል
ሞት ካጠላበት ትልቁ ዋርካ
የህይወት ችግኝ ብልጫ አለው
በጨለማ ካለ የማያልቅ አምሮት
ብርሃን ብቻውን አርኪ ነው
የእግዚአብሄር የሆነው
ጥቂቱ ይበቃል
ሰው ለከንቱነት
እንዲሁ ይጨነቃል /2x
ለራስ ለስጋ ከሚሸጥ ነፃነት
የፍቅር ባርነት ይበጃል
በግፍ በዕብሪት ከዳበረ እኔነት
የትሁት ራስ መካድ ይሻላል
ትርጉም ለሌለው ለውሸት ከመኖር
ለእውነት መሞት ክብር ነው
መጽሃፍ እንደሚል የእግዜር ሞኝነት
ከሰዎች ጥበብ ጠቢብ ነው
ለሙት ትርፍ ህይወት ቢከፈል
ምን ትርጉም አለው?
ስጋችን በቃኝ አያውቅም
ጥበብ በመገራት ነው
ጣፋጩን መብል ፍለጋ
ኑሮን ከማምረር
ዋናውን በልብ አንግሶ
ህይወት ማሳመር
የእግዚአብሄር የሆነው
ጥቂቱ ይበቃል
ሰው ለከንቱለት
እንዲሁ ይጨነቃል /2x
ንፁውን መልካሙን መውደድ (መውደድ)
ቅዱሱን ፍፁሙን መፈለግ
ከዓለም ከንቱ ክምችት
ጥቂቱን በቂውን መሻት