Рет қаралды 161,692
አሜሪካ ብዙ አመት በግ ዶሮ ሲገበርልኝ ኖርኩ ደም ሲፈስ ደስ ይለኛል በጣም አፈቅራታለሁ ግን እሷበመቁጠሪያ እየቀጠቀጠችኝ ነቃችብኝ እባክህ አትሸኘኝ
እያለ በቁጭት የተሸኘው መንፈስ
ስለዚህ ምን ይሻላል? ክርስቲያንም ሆነን አረማዊም ሆነን እንኖር ዘንድ እንደምን ይቻለናል? አሁን አንደኛው ፈተና የሆነብን ጉዳይ እኮ ዛሬ ዛሬ መንፈሳዊነትን ከአረማዊነት አግባብቶ ለመያዝ በሚደረገው ትግል ውስጥ ቢነግሩት የማይሰማ፣ ቢመክሩት የማይገሰጽ፣ ቢቀሰቅሱት የማይነቃ፣ ቢለምኑት የማይቀበል ሞገደኛ ጠባያትንና የውስጥ አመልን አበልጽገን ይዘን፤ በጎ ሲነገረን፣ ስናይ እና ሲደረግ አይስማማንም፡፡ ቢስማማንም አንሳተፍም፡፡ ራቅ ብለን እናያለን፡፡ ከሩቅ በመመልከታችን ክፍተት ውስጥ ታዛቢ ስንሆን፤ ለማፍረስ የሚቸኩል ስብዕና፣ ለመተቸት የሚሮጥ ቋንቋ፣ ለመጣል የሚሮጡ እግሮች፣ ለመገፍተር የሚፋጠኑ እጆች የመያዝ አዝማሚያዎችን እንደ ጋራ ጠባይ ስናስተናግድ ለምን ብለን አንጠይቅም፡፡ ታዲያ እንዴት ነው ነገሩ? ለምንድነው የምንደበላለቀው? ለምንድነው ረግቶ መቆየት የተሣነን?
ነጭ አርጎ የሰጠን ላይ ጥቁር እየለወስንበት፣ በጎ ቃልን እንድንናገር የከፈተልንን አንደበት ነገርና ክፋትን ጨምረን አሰልጥነን ይዘን፣ ፍቅራችን ውስጥ ጥላቻ፣ እውቀታችን ውስጥ ምቀኝነት፣ ገንዘባችን ውስጥ ግፈኝነት፣ ምገሳችን ውስጥ አመፀኝነት፣ ችሎታችን ውስጥ ጨቋኝነት፣ ጸጋችን ውስጥ ተንኮለኝነት፣ ጥበባችን ውስጥ አጥፊነት አቀላቅለን ይዘን ለሌላውም ስናቀርበው ይህንኑ የተደባለቀ ባቢሎንነትን ከትውልድ ትውልድ፤ ከዘመን ዘመን እያሸጋገርን አምጥተን የምንጓዝበት ጓዳና ሁሉ ወደ መከነው እያደረሰን፤ አንዱን ስንለው አንዱ፣ ተስተካከለም ስንለው እየተደመሰሰ፣ ጠራ ስንል እየደፈረሰ፣ አማረበት ሰንል እየጠወለገ ግልብጥብጡ የወጣ ዘመንና አኗኗር ላይ መቆማችንን ስንመለከት በእርግጥም ሳንጠራጠር 'መካን በዘመኑ ሁሉ የማይከናወንለት ሰው ብለህ ጻፍ' የሚለው የነብዩ ኤርሚያስ ትንቢት የኛ ገጽታ እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡
ስለዚህ ምን ይሻለናል? እንዴት ነው ነገሩ? ምን እንወስን?
Subscribe, Share, Like, Comment እያደረጋችሁ ላልሰሙት አሰሙ ላልነቁ አንቁ! መንፈሳዊነት ይብለጥ! የማዳመጥ ጊዜ ላይ ነን!!!