Рет қаралды 2,893
#apostolicchurchofethiopia #apostolicsongs #lyrics #ethiopia
ስጠራህ ትመልስልኛለህ
እኔ የማላውቀውን ታላቅ ነገር ኢየሱስ ታደርጋለህ
ሩቅ አይደለህም ኢየሱስ ቅርብ ነህ
ስጠራህ ሰምተህ ትመልሳለህ
1) የምታስደንቅ ሁሌ በማዳን
አይታጣህም አንዳችስ እንኳን
የኤልያስ አምላክ እንደ ትናንት
ትመልሳለህ ሰምተህ በእሳት
እንዲህ ነው እንዲያ አትባልም
መንገዱን ማንም አይነግርህም
ለኔ የከበደው ባንተ አይን ቀሎ
አይቻለሁኝ ሁሉ ተችሎ
ሩቅ አይደለህም...
2) የሞተውንም የምታስነሳ
መከራን ሁሉ የምታስረሳ
ዘመናት ቢያልፍ ጊዜ ቢቆጠር
ዛሬም በብርታት አለህ በክብር
በእንግዳ ስራህ እያስደነከኝ
አዲስን ነገር ከፊት አለ አልከኝ
በሚሆነውም ልቤ እንዳይዝል
አለህ ከኔ ጋር እንደ ኃያል
ስጠራህ…
አንተን ጠርቼ እኔ አላፍርም የሱስ
ስምህን ይዤ ከቶ አልወድቅም
የማልችለውን ታሻግረኛለህ በጠላቴ ራስ ላይ ታቆመኛለህ
በድል ላይ ድል አንተ ትሰጠኛለህ/4*