Рет қаралды 253,742
#Subscribe_Share_like_በማድረግ_አገልግሎቱን_ይደግፉ። ብዙ ጊዜ ሰዎች ስለ ክፉ መንፈስ አሠራር ተምረው ጠላታቸውን መዋጋት ከጀመሩ በኋላ "እኔ አቅም የለኝም ደካማ ነኝ፣ በጸሎታችሁ አስቡኝ እኔ አቃተኝ፣ እኔ ማድረግ አልችልም እርሱ ይርዳኝ እንጂ" የሚል ከውጪው የእግዚአብሔርን ክንድ ድጋፍ የሚጠይቅ ከውስጡ ግን አውቆ የተኛ ልፍስፍስነትን የሚደብቅ ድምፅ ያሰማሉ፡፡ የውስጥ ስሜታችንን፣ ልባችንን፣ ፍቃዳችንንና አካሄዳችንን ውስጣችን ስላደረ ማንበብ የሚችለው የዲያብሎስ መንፈስ፤ እነዚህን ቀድሞ የመሸነፍ ቃላት እንደ ቀብድ አድርጎ ለግብሩ በመውሰድ የበለጠ ልፍስፍስነት፣ የበለጠ አልችል ባይነት፣ የበለጠ አቅመ ቢስነት እንዲሰማን የማድረግ ዕድልን ከአንደበታችን ላይ ተርጉሞ ይወስዳል፡፡
ውጊያ ላይ ሆኖ፤ ጠላትን የሚደመስስ ከባድ የጦር መሣሪያ ታጥቆ፤ በየዕለቱ በመበርታት ባላጋራን የማጥቂያ መንገዱን አውቆ "አይ ደከማ ነኝ፥ አልችልም" እያሉ ማፈግፈግ በከባዱ መሣሪያ ደንግጦ የነበረውን ኃይል የሚያበረታ ሲሆን፤ በድፍረት ይጠጋም ዘንድ ምልክት የሚሰጥ አካኋን ነው፡፡
የክርስቶስ ወታደሮች ነንና እኛም ጠላታችን ዲያቢሎስን በዕለት ዕለት የአምልኮት ስግደት፣ ጸሎትና መቁጠሪያ እያደከምነው፤ በቅዱስ ቁርባን እየደመሰስነው፤ ፈተናውን ሁሉ እንደ እምነት ማበልጸጊያነት ለመጠቀም የምንችልበት የአምልኮት መንገድ ላይ ቆመን "አይ እኔ እንዲህ ነኝ፣ እንዲህ ስለሆነ እኮ ነው፣ በዚህ ምክንያት ነው እኮ" ብለን የምንሰጠው የማፈግፈግ ሰበብ፤ ፈርተውን የነበሩትን ክፉ መናፍስት ጉልበት የሚሰጥና እንደገና አንሰራርተው ስልት በመቀየር እንዲዋጉን አቅም የሚሆን ሁኔታ መሆኑን ማወቅ አለብን፡፡
በዚህም የመናፍስቱን አሳብ ለመቆጣጠር የምናደርገው የውጊያ ሂደት የራሱ ጊዜ፣ የራሱ ውጥረት፣ የራሱ ድካም፣ የራሱ ደስታ፣ የራሱ ድል እንዳለው አውቀን፤ በየቀኑ እንበረታ ዘንድ የነፍስ ፍላጎት ከሌለን፤ ስልቱን ብንማረውም ሳምንት ተዋግተን ወደነበርንበት እንመለሳለን፡፡ ስለዚህ በቀኑ መጀመሪያና መጨረሻ ላይ የበረታ የውጊያ አቋማችንን ከስነልቦና፣ ከአካልና ከመንፈሳዊ እድገት አንጻር እየፈተሽን የምንደክምበትን ክፍል ለማስተካከል፥ የምንጠነክርበትን ቦታ ለማጥበቅ የጥሞና ጊዜን ለራሳችን በመስጠት በየቀኑ መታደስ አለብን፡፡