Рет қаралды 80,387
#Subscribe_Share_like_በማድረግ_አገልግሎቱን_ይደግፉ።
ከዘመናት አስቀድሞ እኛ ወደ ምድር ከመወረዳችን በፊት መሬትን የተቆጣጠሩት የርኩሳን መናፍስት ነገድ፤ እኛን ከማሳደድ ውጪ አንዳች ሌላ ሥራ የላቸውምና፤ እግዚአብሔር በተለየው ኑሮአችን ላይ ኑሮ ሆነው፥ በሥጋ ዓይን አለመታየታቸውን ተጠቅመው፣ በሥጋ አእምሮ አለመታወቃቸው እጅጉን ጠቅሞዋቸው፤ ዛር እየሆኑ አብረው በመወለድ፣ ቡዳ እየሆኑ ከሰው ላይ በመግባት፣ መተት እየሆኑ ለጥፋት ወደኛ በመላክ፣ ዓይነጥላ እየሆኑ ዕድላችንን በመጋረድ፤ እየኖርን የሚመስለን ሙታን እንድንሆን የነፍሳችንን ኃይል በስግደትና በጸሎት እንዳናወጣው ተመሳስለው ሰውነታችን ውሰጥ አድረው፥ ባሕሪያችንን ፍጹም ከመንፈሳዊ እውነትና ኃይል ስላራቁት፤ ወይ አንደኛውን እንደ ውጪው ዓለም እግዚአብሔርን ሙሉ በሙሉ ከድተን የሥጋ ትርፋማ አልሆንን፥ ወይ እግዚአብሔርን በሙሉ ኃይል ተቀብለን የነፍስም የሥጋም ትርፋማ አልሆንን፤ በሰማይም በምድርም ስቃይ የሚከበን ፍጥረቶች ሆነን ተይዘን ቁጭ ብለናል፡፡
ታዲያ ምን ይሻላል? እስከመቼ ግራ ግብት እንዳለን እንቆያለን? እስከመቼ ተሰቃይተን እንዘልቃለን? እስከመቼ ሃይማኖትን ከአንደበት አሻግረን ለመኖር እንደሸሸን እንቀጥላለን? እስከ መቼ ሕይወታችን ውስጥ ፍጹም እኛን ሆነው ያሉትን መናፍስት ሳንከላከል ተሸንፈን እንኖራለን?
በእውነት እግዚአብሔር የውስጥ ልቦና ይስጠን፡፡ የጸሎት ቤት ሲኖረን፤ እግዚአብሔርን ጠዋት ማታ ለማግኘት የምንችልበትን ቅርብ የኑሮ ጊዜ እናገኛለን፡፡ አምላክ ሰንበት ሰንበት ሲሆን ብቻ ቤተክርስቲያን ሄደን የምናገኘው የሰሞን አባት አይደለም፡፡ በቀኖቻችን ላይ ሁሉ አብሮን እንዲኖር ሁሌ በምንገኝበት ቦታ ላይ መንበርከኪያ ማበጀት ያስፈልገናል፡፡
የዘመኑ ክርስቲያኖች፤ ትልቅ መንፈሳዊ ጉዳት ሆኖብን የሥጋም የነፍስም ድኩማኖች እንድንሆን የተገደድንበት ምክንያት እግዚአብሔርን የምናገኝበት ጊዜን በሰሞን በመወሰናችን ነው፡፡ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ የተቀደደ ጅንስ ለብሰን፥ እሁድ ላይ ቤተክርስቲያን በነጠላ ተከልለን እንሄዳለን፡፡ ከሰኞ እስሰ ቅዳሜ ሐሜትና ክፉ ስናወራ ቆይተን፥ እሁድ ጠዋት አንተ ታውቃለህ ልንል ቤተክርስቲያን እንሄዳለን፡፡ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ብዙ ኃጢአቶችን ያለ ሕሊና ወቃሽነት ስንፈጽም እንቆይና፤ እሁድ "ቃለ ሕይወት ያሰማልኝ!" ልንል ቤተክርስቲያን እንሄዳለን፡፡ ከሰኞ እስከ ቅድሜ ያሻንን እንደፈልግን ስናደርግ እንቆይና፥ እሁድ ላይ "እንደ ፈቃድህ ልኑር" ደግሞ እንላለን፡፡ ስለዚህ በዚህ ሁኔታ፥ እሁድ ቀን ላይ፣ የንግሥ በዓል ላይ፣ ገዳም የምንሄድ ጊዜ ላይ፣ ሰው ያወራልን ቀን ላይ ብቻ ክርስቲያን እየሆንን፤ አብዛኛውን የሕይወታችንን ክፍል ውስጣችን እንደመራው፣ ሥራችን እንዳዘዘው፣ አጋጣሚው እንዳመጣው ስንኖር፤ ጠዋት ማታ በቤታችን ያልተንበረከክንበት ጊዜ የዲያቢሎስ መረብ ውስጥ ገብተው የሚሰቃዩ እስረኞች አድርጎን ሁለት ሞት ለመሞት የሚኖሩ ተንከራታቾች ለመሆን የተፈረድብን መስለን እንመላለሳለን፡፡